· በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከአማራ ፋኖ በጎንደር የተሰጠ መግለጫ!

ለተከበርከው የአማራ ሕዝብ በሙሉ!

የአማራ ህዝብ ካለፈው 40 አመት የቀጠለ ጥቃት በብልፅግና ስርዓት ቀጥሏል የአማራ ህዝብ በደሙ በአጥንቱ በገነባት ሀገር ውስጥ ሀገር አልባ እና ተሳዳጅ ተደርጎ ባይተዋር ሆኗል፤ ይህ የዛሬ እውነት ነው። እንዲሁም የመዋቅራዊ ጭቆና ውስጥ ገብቷል። ይህን ጭቆና አድራጊዎች ደግሞ ትናንት የህዋሀትን አምባገነናዊ ስርዓትን ለመገርሰስ አብረናቸው ስርዓታዊ ለውጥ ለማምጣት እና እኩልነት ለማስፈን የታገልነው የዛሬዎቹ ተረኞች የኦህዴድ /ኦሮሙማ/ ተረኛ አምባገነናዊ መሪዎች ናቸው።

ስለዚህ የአማራ ፋኖ በጎንደር ይህን አምባገነናዊ ስርዓት ጭቆና ለመገርሰስና እስከ ወዲያኛው መቀመቅ ውስጥ ለመክተት ለተከበርከው የአማራ ህዝብ የሚከተሉትን የአቋም መግለጫዎች ማሳዎቅ ይፈልጋል:-

፩ኛ. ለመላው የአማራ ሕዝብ፦

ለተከበርከው በሸዋ በወሎ በጎጃም በጎንደር እንዲሁም በመላ ሀገሪቱ የምትገኝ ህዝባችን እየተደረገብህ ያለውን መዋቅራዊ ጥቃትና ማሳደድ በወል ተረድተህ፤ ለመጨረሻው መጀመርያ ሁሉን አቀፍ ትግል እራስክን እንድታዘጋጅና እንድትነሳ እንዲሁም በጎጥ ሊከፋፍሉህ ከሚሞክሩ የውስጥም የውጭም ጠላቶችህን አጀንዳ ወደ ጎን በመተው አሁን እያደረክ እንዳለህው አንድ አማራዊ ስነ ልቦና ጥቃት አደራሹንና ሴራ ጠማቂውን ፀረ አማራ የብልፅግና አገዛዝ ስርዓትን በፅኑ እንድታገል ስንል በጥብቅ ማሳሰብ እንፈልጋለን።

በተጨማሪም ከአብራክህ የወጣውን የቁርጥ ቀን ደራሽ የሆነውን የፋኖ አደረጃጀት በሞራል በግብዕት በትጥቅና ስንቅ አብረህ ለመታገል ቁርጠኛ አቋም እንድትይዝ ስንል በድጋሚ አማራዊ ጥሪያችን እናስተላልፍልሃለን።

፪ኛ. ለመላው አማራ ፋኖ፦

ትናንት የከፈላችሁትን መሰዋዕትነት ለዛሬ የአማራ ህዝብ በዚህ ሁኔታ ለመገኘቱ ትልቅ አስተዋዕፆ አለው። ይህ በእንዲህ እንዳለ በሁሉም አካባቢ ለምትገኙ የአማራ ፋኖ አደረጃጀትና አባላት የሚከተሉትን መልዕክቶች ማስተላለፍ እንፈልጋለን።

~ ሀሳዊያን ፋኖ ነን ባዮች ቀንደኛ የአማራ ህዝብ ጠላት የሆነውን የብአዴን ቅጥረኞች ሰለባ እንዳትሆን እራስክን ከእውነተኛ የህዝብ ልጅ ከሆኑት ከአስራታዊያን ከጎቢያዊያን እንዲሁም ከአሳምነው እውነተኛ የህዝብ ልጆች ጋር በማድረግ እንድትታገልና እራስክንም መከራ የበዛበት ህዝብህንም ከተጋረጠበት ባርነት ነፃ እንድታዎጣ ስንል እናሳስባለን። እንዲሁም በጊዚያዊ ጥቅም ተታለህ እራስክን ሁሌም በአዴን ሰራሽ ለሆነ ርካሽ የፖለቲካ ፕሮፖጋንዳ ተጋላጭ ሳትሆን ፍፁም ልክ በሆነ አማራዊ ስነልቦና በመነሳት ህዝባዊ ትግል እንድታደርግ እንዲሁም ሁሌም ዝግጁ በመሆን እራስክን በአካላዊና ስነ ልቦናዊ ጥንካሬ እንድትጠብቅ ስንል ጓዳዊ ጥሪ እናቀርብልሃለን።

፫ኛ. ለአማራ ህዝብ ማህበራዊ/ሀይማኖታዊ / ተቋማት፦

እንደሚታወቀው የኦሮሙማ ሰልቃጭ/አውዳሚ / ስርዓት ፖለቲካዊ ሁኔታዎችን አልፎ የመጨረሻ የህዝብ የደም ስር የሆነውን የሀይማኖት ተቋማት መድፈሩ የአደባባይ ሚስጥር ከሆነ ውሎ አድሯል። ይህን እውነታ ሲኖዶስን በማፍረስ መጅሊስን በመከፋፈል ሁሉም የኦሮሙማ የፖለቲካ ሀይሎች ሲተባበሩ አይተናል። ይህ አልበቃ በማለት ይህ የኦሮሙማ ስርዓት ጠባቂ የሆነው የመከላከያ አባላት በጓጃም በደብረ ኤልያስ ገዳም በከባድ መሳርያ የታገዘ ጥቃት በመክፈት ከ550 በላይ መነኮሳትን በግፍ በመጨፍጨፍና ጥንታዊ ቅርሶችን በማውደም እንዲሁም የሸገር ከተማ ማቋቋም በሚል ተረኝነት በርካታ መስጊዶችን አለም እያየ በግፍ አውድሟል።

ይህን እምነት አልባነት አላማው ያደረገው ስርዓት ወደ ጥንታዊቷ ጎንደር በመጓዝ ጓርጓራ ደብረ ሲና ማርያምና ማን እንደ አባ ጥንታዊ ገዳማት አጥቢያዎች ውስጥ ፀረ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ ሚኒስትሮችንና የክልል ባለስልጣናትን ብሎም የኦነግ ወታደራዊ አመራሮችን በመሰብሰብ /ጭፈራናድግስ/ በማዘጋገት ፍፁም በማን አለብኝነት የህዝብ እና የእምነት ተከታዩን ስነ ልቦና በሚጓዳ መልኩ በፆም ቀን የእርድ ተግባር በመፈፀም ማን አለበኝነቱን አሳይቷል። ይህን አስነዋሪ ድርጊት ሲፈፅም የተቃወሙትን የሀይማኖት አባቶችና የአካባቢው ገበሬዎች ላይ የዘር ማጥፋት ሊባል በሚችል ደረጃ ለሚያምነው/ለሚገብረው/ የደም ግብር መሰዋዕት ተደርገዋል።

ስለዚህም ይህን ጥቃት ለመመከትና ለመቀልበስ በሚደረገው ህዝባዊ ትግል ማህበራዊና ሀይማኖታዊ ተቋማት በግልፅ እንድትቃወሙና ድጋፍ እንድታደርጉ ጥሪ እናስተላልፋለን።

፬ኛ. ለአማራ ብልፅግና አባላት፦

ትናንት ብአዴን ሆናችሁ ለህውሀት ተላልካችሁ የአማራን ህዝብ አንገት በማስደፋትና ርስቶችን አሳልፋችሁ በመስጠት ያደረጋችሁት በደል ሳይደርቅ፤ ዛሬ ደግሞ በደምና በአጥንቱ መስዋዕትነት ያስመለሳቸውን የወልቃይት ጠገዴ እና ራያ አካባቢዎች በህግ አግባብ ሳይመለሱ አምነንና ትናንት ያደረጋችሁትን ግፍ ለታሪክ ትተን መሪ አርገናችሗል ሆኖም ግን ከትናንት ያደረው የተላላኪነትና የክህደት እንዲሁም ራስን ችሎ ያለ መቆም መንፈስ ተጠናውቷቹሁ ዛሬም ከትናንቱ የቀጠለው ክህደታችሁ በባሰ መንገድ ቀጥሏል።

ለዚህም ማሳያ፦

~ ከ500 000 በላይ አማራና ሌሎች ወንድም ኢትዮጵያዊያን ጥረው እና ግረው ያፈሩትን ሀብት ንብረት በአንድ ጀንበር በተረኞች ሲነጠቁና የጅብ ሲሳይ ሲሆኖ ለሆዳችሁ ስትሎ ጆሮ ዳባ ልበስ በሚመስል መልኩ ዝም ብላችኋል ።

~የኦሮሙማ ጌቶቻችሁን ለማስደሰት የአማራ ህዝብ ልጆቹን አዋጦ ጥሪቱን አሟጦ የገነባውን የአማራ ልዩ ሀይል አፍርሳችሁ ጠባቂ አሳጥታችሁ የጠላቶቹ መጫዎቻና መፈንጫ አድርጋችሁታል።

~ የአማራ ህዝብ ለመዋቅራዊ ጥቃት እንዲጋለጥና እራሱን ችሎ እንዳይቆም በራሳችሁ የጥቅም ፖለቲካ ሴራ ውስጥ አስገብታችሁ በጎጥ የአስተሳሰብ ገመድ እንዲጓተት ጊዜና በጀት በመመደብ ለማሻኮት ጥረት በማድረግ ላይ ትገኛላችሁ ይህን የምታደርጉት ህዝባችን ፖለቲካዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች በራሱ መንገድ እንዳይመለሱ ፍፀም በፍርሀት ቆፈን ለማስገባት እያደረጋችሁት ያለው ከንቱ ጥረት ይታወቃል።

ሆኖም ግን ዛሬ ትናንት አይደለምና አሁናዊ እውነትን ተረድታችሁ ከመሸም ቢሆን ለአማራ ህዝባዊ ትግል መርህ ተገዢ በመሆን የአማራ ህዝብ የህልውና ትግል እንቅፋት እንዳትሆኑ ስንል ጥሪ እናስተላልፋለን።

፭ኛ. ለአማራ ሚሊሻ፣ ፖሊስ/አድማ ብተና / አባላት፦

ልክ እንደ እናንተ ሁሉ የአማራ ፋኖ የአማራ እናትና አባት የወለደው የህዝብ ልጅ ነው ሆኖም ግን ህግ ማስከበር በሚል ሰበብ በፋኖ ወንድሞቻችሁ ቃታ እንድትስቡእና ህዝባዊ መጠፊፊት እንዲደርስ በተደጋጋሚ ስልጠናና ተልዕኮ እንስጣችሁ በሚል ተረኞቹ የሸረቡትን ሴራ አክሽፋችሗል በዚህም ህዝቡም ፋኖም ኮርቶባችሗል ከዚህ በመነሳት በቀጣይም ፋኖ አማራ ለሚያደርገው ህዝባዊ ትግል የበኩላችሁን አስተዋዕፆ እንደተለመደው እንድታደርጉ ስንል እንገልፃለን።

፮ኛ. ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት / ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን /

በውል ለመተንበይ በሚያዳግት ሁኔታ ሀገራችን ውስብስብ ወደ ሆነ የለየለት አምባገነናዊ ስርዓት ገብታለች ለዚህ ማሳያ ሀገርን ከወንድም ህዝቦች ጋር ያቆመው የአማራ ህዝብ እየደረሰበት ያለውን ጭፍጨፋ ማሳደድ እና ሀገር አልባ ማድረግ በቅርብ እንደ አስፈፃሚነት ስለምታውቁት ለእናንተ መንገር ለቀባሪ ማርዳት ይሆናል።

በመሆኑም የአማራ ህዝብ የራሱን ህልውና መሰረት አድርጎ ኢትዮጵያን ከመበተን ለመጠበቅ ለጀመረው የህዝባዊ ትግል አጋርነታችሁን እንድታሳዩ ጥሪ እናስተላልፋለን።

፯ኛ. ለአማራ ህዝባዊ ተጋድሎ ታጋዮች እና አስተባባሪዎች፦

ሀገራችን የገባችበትን ምስቅልቅልና መቀመቅ በወል በመረዳት ከፍረጃ በፀዳ አካባቢያዊነትና ሉላዊነትን በጠበቀ የተተነበየ የአማራን ህዝብ ትግል ለስኬት የሚዳርግ ትግል እንድናደርግ ዛሬ ከትናንት በበለጠ ለህዝባችሁ ታስፈልጋላችሁ እናም ላለው አምባገነን ዘረኛ ስርዓት ሰለባ ሳትሆኑ የአማራ ህዝብ ለጀመረው የህልውና ና ኢትዮጵያን ለማዳን ለሚደረገው ትግል የበኩላችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን።

፰ኛ. ለዲያስፖራ ማህበረሰብ፦

በተሳሳተ መረጃና በማህበራዊ ገፅ ፕሮፖጋንዳ ለብአዴናዊያን ሴራ ሳትጋለጡ የአማራ ህዝብ ትግልን በቀናነት በመደገፍ ትግል በሁሉም ዘርፍ ነውና የአማራ ህዝብ እየደረሰበት ያለውን የዘር ፍጅት ለተቀረው የአለም ህዝብና የሰብዓዊ መብት ጠባቂ ተቋማት በማሳወቅ እንዲሁም የአማራ ፋኖን በመደገፍ ህዝባዊነታችሁን እንድታሳዩ ስንል ጥሪ እናስተላልፋለን።

አማራነታችን በደምና በአጥንት እናፀናለን!!!

ፋኖ አማራ በጎንደር

ሐምሌ 22 ቀን 2015 ዓ.ም

ጎንደር፤ ኢትዮጵያ