August 21, 2023 – Konjit Sitotaw
1. ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ተሹመዋል። የኢንተርፕራይዞች ሃላፊ የነበሩ ሲሆን የርዐሰ መስተዳደር ይልቃል ከፋለን ቦታ ተረክበዋል።
2. ደሳለኝ ጣሳው የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ ሲሾሙ የሰማ ጥሩነህን ቦታ ተክተዋል። ሲሰሩ የነበሩበት የክልሉ ጸጥታ ሃላፊ በመሆን ነበር።
3. ዶ/ር ድረስ ሳህሉ የባህርዳር ከተማ ከንቲባ የነበሩ ሲሆን የስዩም መኮነንን ቦታ በመረከብ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሆነዋል።
4. ዶ/ር ጋሻው አወቀ የብልጽግና የፓለቲካ ዘርፍ ሃላፊ የነበሩ ሲሆን የዶ/ር ጌታቸው ጀምበርን የምክትል ርዕሰ መስተዳደር ቦታ ተረክበዋል።
5. አቶ ይርጋ ሲሳይ የብልፅግና ፓርቲ በነበሩበት እንዲቀጥሉ ተደርገዋል።
6. ዶ/ር አብዱ ሁሴን በነበሩበት የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ ሆነው እንዲቀጥሉ ተብሏል።
የቀድሞ ባለስልጣናቱ በወጡበት አዲስ አበባ ቀርተዋል። ኮማንድ ፖስቱ መግለጫ ለመስጠት ዛሬ ወይ ነገ ዝግጅቱን ጨርሷል።