ቀጥታ
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታኒያሁ የአስቸኳይ ጊዜ መንግሥት እና የጦርነት ካቢኔ አቋቋሙ
Related Video and Audio

VIDEO 1 MINUTE 33 SECONDSVIDEO 1 MINUTE 33 SECONDS1:33
Play video በእስራኤል እና በሐማስ መካከል የተፈጠረው ግጭት የመጀመሪያዎቹ ክስተቶች from BBCበእስራኤል እና በሐማስ መካከል የተፈጠረው ግጭት የመጀመሪያዎቹ ክስተቶች
- BBC
Play video በእስራኤል እና በሐማስ መካከል የተፈጠረው ግጭት የመጀመሪያዎቹ ክስተቶች from BBC

VIDEO 1 MINUTE 23 SECONDSVIDEO 1 MINUTE 23 SECONDS1:23
Play video ሐማስ በእስራኤል ላይ የከፈተው ድንገተኛ የተቀናጀ ጥቃት እንዴት ጀመረ? from BBCሐማስ በእስራኤል ላይ የከፈተው ድንገተኛ የተቀናጀ ጥቃት እንዴት ጀመረ?
- BBC
Play video ሐማስ በእስራኤል ላይ የከፈተው ድንገተኛ የተቀናጀ ጥቃት እንዴት ጀመረ? from BBC
ጭምቅ ሃሳብ
- በአራት ቀናት ውስጥ ከ260 ሺህ በላይ ፍልስጥኤማውያን ከጋዛ ተፈናቅለዋል፡ የተባበሩት መንግሥታት
- ኢራን በእስራኤል ላይ ለተፈጸመው ጥቃት ድጋፏን ሰጥታ ይሆን?
- የፍልስጥኤማውያን የተቃውሞ ሰልፍ በዌስት ባንክ
- የቀጠለው የእስራኤል ጥቃት እና የአውሮፓ ኅብረት ትችት
- እስራኤል ከሶሪያ በኩል ለተሰነዘረ ጥቃት አጸፋውን መመለሷን ገለጸች
- የሳዑዲው ልዑል ሞሐመድ ቢን ሳልማን ለፍልስጥኤማውያን ድጋፋቸውን ገለጹ
- ውጊያው ሳይቆም በታጋቾች ጉዳይ ላይ አንደራደርም፡ ሐማስ
- በእስራኤል እና በሐማስ መካከል የተፈጠረው ግጭት አጀማመር ምን ይመስላል?
- በጋዛ ከ123 ሺህ በላይ ፍልስጥኤማውያን ተፈናቀለዋል
- ኢራን፣ ሐማስ በፈጸመው ጥቃት ላይ ተሳትፎ የለኝም አለች
- እስራኤል በሊባኖስ ላይ በከባድ መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ፈጸመች
ቀጥታ ዘገባ
- የታተመዉ 13:5813:58‘የት እንሂድ?’ የጋዛ ነዋሪዎችን መሸሸጊያ አልባ ያደረገው የተጠናከረው የእስራኤል ጥቃትየእስራኤል ጥቃት በርካታ የመኖሪያ ሕንፃዎችን አውድሟል። የቴሌኮሙኒኬሽን ኩባንያ ቢሮዎች እና የጋዛ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ሕንጻም ክፉኛ ተጎድተዋል። ሰኞ ዕለት አስፈሪ ፍንዳታዎች አካባቢውን ሲንጡ አመሹ። ልጆች ያለቅሳሉ፤ ለደቂቃዎች ማሸለብ የቻለም የለም።ተጨማሪ ያንብቡArticle share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 10:5810:58ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታኒያሁ የአስቸኳይ ጊዜ መንግሥት እና የጦርነት ካቢኔ አቋቋሙ
OREN ROSENFELDCopyright: OREN ROSENFELDበስምምነቱ ከሐማስ ጋር የሚካሄደውን ጦርነት የሚመራ ካቢኔ ተቋቁሟልImage caption: በስምምነቱ ከሐማስ ጋር የሚካሄደውን ጦርነት የሚመራ ካቢኔ ተቋቁሟልየእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ እና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪው ቤኒ ጋንትዝ የአስቸኳይ ጊዜ መንግሥት ለማቋቋም ተስማሙ።ሁለቱ ፖለቲከኞች እዚህ ስምምነት ላይ የደረሱት ሐማስ ድንገተኛ ጥቃት ከፈጸመ በኋላ እስራኤል መጠነ ሰፊ የአጸፋ እርምጃ በጋዛ ላይ እያካሄደች ባለበት አምስተኛ ቀን ላይ ነው።ይህንን ስምምነት ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታኒያሁ፣ ጋንትዝ እና የአገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር ያሉበት “የጦርነት ካቢኔ” ያቋቁማሉ ተብሏል።በስምምነቱ መሠረት ጦርነቱ በሚካሄድበት ጊዜ “የጦርነቱን ሂደት ከሚመለከቱ ጉዳዮች በስተቀር ማንኛውም አይነት ሕግም ሆነ የመንግሥት ሃሳብ ለውሳኔ አይቀርብም።”በተጨማሪም ከዚህ ቀደም ከፍተኛ የመንግሥት ሥልጣንን እንዲይዙ የተሾሙ ሰዎች የኃላፊነት ጊዜ በጦርነቱ ወቅት ሁሉ የሚቀጥል ይሆናል።ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታኒያሁ እና የናሽናል ዩኒቲ ፓርቲ ሊቀ መንበር ጋንትዝ የአስቸኳይ ጊዜ መንግሥት ለማቋቋም የተስማሙት ላለፉት ቀናት ንግግር ካደረጉ በኋላ ነው።ከስምምነቱ በኋላ ከሁለቱም ወገን በጋራ በወጣ መግለጫ ላይ “የአስቸኳይ ጊዜ መንግሥት ለመመሥረት እና ጦርነቱን የሚመራ ካቢኔ ለማቋቋም ተስማምተዋል።“ጦርነቱን የሚመራው ካቢኔም ጠቅላይ ሚኒስትሩን፣ የመከላከያ ሚኒስትሩን እና የተቃዋሚ ፓርቲውን መሪ በአባልነት ይዞ ይመሠረታል” ተብሏል።ከሦስቱ ባለሥልጣናት በተጨማሪ የጦርነቱ መሪ ካቢኔን በታዛቢነት የሚያገለግሉ ሁለት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ይካተቱበታል።Article share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 8:598:59ረቡዕ የተከሰቱ ዋና ዋና ጉዳዮች
Getty ImagesCopyright: Getty Imagesየጋዛ ዋነኛ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ማዕከልImage caption: የጋዛ ዋነኛ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ማዕከልእስራኤል በሐማስ ለተፈጸመባት ጥቃት አጸፋ ጋዛ ላይ ከበባ በመጣል ለአምስተኛ ቀን ተከታታይ የአየር ጥቃት እየፈጸመች ሲሆን፣ ሐማስም የሮኬት ጥቃቱን ቀጥሏል።በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የጋዛ ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል።መሠረታዊ አቅርቦቶች በከተማዋ ውስጥ እየተሟጠጡ መሆናቸው እየተዘገበ ነው።ዛሬ ረቡዕ እስካሁን የተከሰቱ ዋና ዋና ጉዳዮች ምንድን ናቸው?
- እስራኤል በጋዛ ላይ በጣለችው ጥብቅ ገደብ የነዳጅ ዕጥረት በመከሰቱ የከተማዋ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ማዕከል ሥራ ማቆሙን ባለሥልጣናት ተናግረዋል።
- ሰኞ ዕለት እስራኤል ወደ ጋዛ የሚገቡ የኤሌክትሪክ እና የውሃ መስመሮች እንዲሁም የነዳጅ አቅርቦትን እንደምታቋርጥ አስታውቃ ነበር።
- የእስራኤል የአየር ጥቃት በጋዛ ላይ ተጠናክሮ በቀጠለበት በአሁኑ ጊዜ በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች ከጥቃት ለመሸሽ ወደ ሆስፒታሎች እና ትምህርት ቤቶች እየገቡ ነው።
- በእስራኤል ሰሜን እና ደቡብ ግዛቶች ውስጥ የሮኬት ጥቃት ማስጠንቀቂያ ደወሎች የተሰሙ ሲሆን፣ ከጋዛ በተተኮሱ ሮኬቶች የቆሰሉ ሰዎች እንዳሉ ተዘግቧል።
- የእስራኤል ጦር 300 ሺህ ተጠባባቂዎችን ጨምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወታደሮችን በጋዛ ድንበር ላይ አሰባስቧል።
- እስራኤል በድንበር በምትጎራበታት ሊባኖስ ውስጥ የሚገኙ የሄዝቦላህ ታጣቂዎች የፈጸሙባትን ጥቃት ተከትሎም ሊባኖስ ግዛት ውስጥ የአጸፋ ጥቃት ፈጽማለች።
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- የታተመዉ 6:516:51በእስራኤል-ፍልስጥኤም ግጭት የአፍሪካ አገራት ምን አቋም ያዙ?
BBCCopyright: BBCባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ የተቀሰቀሰውን ግጭት በተመለከተ የዓለም አገራት የተለያየ አቋማቸውን እያንጸባረቁ ነው።በዚህም በግልጽ ከእስራኤል ወይም ከፍልስጥኤም ጎን መሠለፋቸውን ያሳወቁ አገራት የመኖራቸውን ያህል፣ ከየትኛውም ወገን ሳይቆሙ ገለልተኛ አቋም ያንጸባረቁም አሉ።ከ54ቱ የአፍሪካ አገራት መካከልም ከፍልስጥኤም ጎን የተሰለፉ፣ እስራኤልን የደገፉ፣ ገለልተኛ አቋም የያዙ እና ለጊዜው ዝምታን የመረጡ አገራት አሉ።በዚህ ዝርዝር አስካሁን በይፋ አቋማቸውን ያንጸባረቁ የአፍሪካ አገራት ተካተዋል።Article share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 6:296:29ጋዛ ውስጥ በእስራኤል ጥቃት የተገደሉት ፍልስጥኤማውያን ቁጥር 1,055 ደረሰ
EPACopyright: EPAእስራኤል ጋዛ ላይ እያካሄደችው ባለው የአየር ጥቃት ምክንያት የተገደሉ እና ጉዳት የደረሰባቸው ፍልስጥኤማውያን ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ነው።የፍልስጥኤም የጤና ሚኒስቴር ረቡዕ እኩለ ቀን ላይ ባወጣው መረጃ የተገደሉ ሰዎች አሃዝ 1,055 ሲደርስ፣ ከ5,100 በላይ ሰዎች ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጨምሮ እንዳለው፣ በጥቃቱ ከተጎዱት ሰዎች መካከል 60 በመቶዎቹ ሴቶች እና ሕጻናት ናቸው።ሐማስ ቅዳሜ ዕለት በፈጸመው ጥቃት የተገደሉ እስራኤላውያን 1,200 ሲሆኑ ከ2,700 በላይ የሚሆኑ ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።Article share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 5:495:49እስራኤል በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮቿን ወደ ጋዛ እያስጠጋች ነው
Getty ImagesCopyright: Getty Imagesየእስራኤል አየር ኃይል ጋዛ ውስጥ የሐማስ ናቸው ያላቸውን ኢላማዎች ለአራተኛ ቀን እየደበደበ ባለበት በዛሬው ዕለት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የእስራኤል ወታደሮች ከጋዛ አቅራቢያ ሰፍረዋል።የሐማስ ጠንካራ ይዞታ በሆነችው ጋዛ ላይ እየተፈጸመ ባለው የአየር ጥቃት ምክንያት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የጋዛ ነዋሪዎች መፈናቀላቸው የተዘገበ ሲሆን፣ በነዳጅ ችግር ምክንያት በከተማዋ በሰዓታት ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ይቋረጣል።የሐማስ ተዋጊዎችን ለማደን እና የታገቱ ዜጎቿን ለማስለቀቅ እስራኤል እግረኛ ሠራዊቷን ወደ ጋዛ ታሰማራ እንደሆነ አስካሁን የታወቀ ነገር ባይኖርም፣ አስፈላጊውን ሁሉ እርምጃ እንደምትወስድ አስታውቃለች።የእስራኤል ጦር ሠራዊት ዛሬ ረቡዕ እንዳሳወቀው በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮቹ “የተሰጣቸውን ተልዕኮ ለመፈጸም ዝግጁ ሆነው” ከጋዛ አቅራቢያ ይገኛሉ ብሏል።Article share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 2:472:47የፍልስጥኤማውያን የተቃውሞ ሰልፍ በዌስት ባንክ
Getty ImagesCopyright: Getty Imagesየእስራኤልን ጥቃት በመቃወም ዌስት ባንክ ራማላህ ውስጥ ሰልፍ የወጡ ፍስጥኤማውያንImage caption: የእስራኤልን ጥቃት በመቃወም ዌስት ባንክ ራማላህ ውስጥ ሰልፍ የወጡ ፍስጥኤማውያንዛሬ ረቡዕ ማለዳ ጎህ ሲቀድ ከጋዛ ባሻገር በወረራ በተያዘችው ዌስት ባንክ ውስጥ ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጥኤማውያን እስራኤል በጋዛ ላይ እየፈጸመችው ያለውን የአውሮፕላን ድብደባ በመቃወም ሰልፍ አድርገዋል።የፍልስጥኤም ዜና አገልግሎት እንደዘገበው ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ የፍልስጥኤምን ሰንደቅ ዓላማ እና በጥቃቱ የተገደሉ ሰዎችን ፎቶፍራፎች ይዘው ነው አደባባይ የወጡት።Article share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 2:392:39ኢራን በእስራኤል ላይ ለተፈጸመው ጥቃት ድጋፏን ሰጥታ ይሆን?የሐማስ ታጣቂዎች ከፍተኛ ቅንጅት ታይቶበታል የተባለውን ጥቃት በእስራኤል ላይ መፈጸማቸውን ተከትሎ የኢራን ስም በተደጋጋሚ እየተነሳ ይገኛል። ከዚህም ጋር ተያይዞ ኢራን በጥቃቱ ተሳትፎ ነበራት ወይ? የሚለው ጥያቄ ከተለያዩ ወገኖች እየተመላለሰ የሚነሳ ሆኗል።ተጨማሪ ያንብቡArticle share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 1:271:27የቀጠለው የእስራኤል ጥቃት እና የአውሮፓ ኅብረት ትችት
Getty ImagesCopyright: Getty Images
- ሌሊቱን የእስራኤል አየር ኃይል የጦር ጄቶች የሐማስ የሮኬት ጥቃቶች የሚወነጨፉበት ነው ባለው የጋዛው አል-ፉርቃን አካባቢ ያሉ ከ200 በላይ ኢላማዎች ላይ ድብደባ መፈጸሙን ገልጿል። ይህም ጥቃት ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ የተፈጸመ ሦስተኛው ድብደባ ነው።
- እስራኤል ሌሊቱን ጋዛ ላይ በፈጸመችው የአየር ድብደባ ቢያንስ 30 ሰዎች መገደላቸውን የሐማስ ቃል አቀባይ አስታወቁ።
- የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ጉዳይ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ጆሴፍ ቦሬል እስራኤል በጋዛ ላይ እየወሰደች ያለችው እርምጃ ዓለም አቀፍ ሕግን የጣሰ ነው ሲሉ ተቹ። “እስራኤል እራሷን የመከላከል መብት ቢኖራትም ይህንን ማድረግ ያለባት በዓለም አቀፍ ሕጎች መሠረት መሆን አለበት” ብለዋል።
- የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የሐማስን ጥቃት አጥብቀው ያወገዙ ሲሆን አሜሪካ ለእስራኤል የምትሰጠውን ወታደራዊ ድጋፍ በማጠናከር የመጀመሪያው የጦር መሳሪያ ድጋፍ ማክሰኞ ደቡባዊ እስራኤል ደርሷል።
- የጋዛ ነዋሪዎች “ደኅንነቱ የተጠበቀ መተላለፊያ” እንዲያገኙ ከእስራኤል እና ከግብፅ ጋር እየተነጋገረች መሆኗን የአሜሪካ ብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ጃክ ሰሊቫን ገለጹ።
- አስካሁን ከፍልስጥኤም እና ከእስራኤል ወገን የሞቱት ሰዎች አሃዝ በአጠቃላይ ወደ 2,100 ሲደርስ፣ ከእስራኤል በኩል 1,200፣ ከፍልስጥኤም ወገን ደግሞ 900 ሰዎች ተገድለዋል።
- በጥቃቶቹ የደረሰው ጉዳት ታይቶ የማይታወቅ መሆኑን እስራኤላውያን እና ፍልስጥኤማውያን እየተናገሩ ነው። እስራኤላውያን “በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈጸመ ጭፍጨፋ ነው” ሲሉ፣ ፍልስጥኤማውያን ደግሞ “ሕይወታችንን የምናድንበት ቦታ አጣን” እያሉ ነው።
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- የታተመዉ 1:011:01እስራኤል ከሶሪያ በኩል ለተሰነዘረ ጥቃት አጸፋውን መመለሷን ገለጸችየእስራኤል ጦር ሠራዊት ከሶሪያ በኩል ወደ ጉላን ተራሮች ለተሰነዘረ የከባድ መሳሪያ ጥቃት በመድፍ ተኩስ ምላሽ መስጠቱን ገለጸ።የጎላን ተራሮች የ1967ቱን የአረብ እስራኤል ጦርነትን ተከትሎ እስራኤል አስካሁን ድረስ በወረራ የያዘቻቸው መሆኑ ይታወቃል።የእስራኤል ጦር ባወጣው መግለጫ ከሶሪያ በኩል የተሰነዘረውን የከባድ መሳሪያ ጥቃት ተከትሎ “ወታደሮቻችን መድፍ እና ሞርታር ጥቃቱ ወደ ተነሳበት ስፍራ በአጸፋው ተኩሰዋል” ብሏል።ጨምሮም ቀደም ሲልም በርካታ ጥቃቶች ከሶሪያ በኩል ወደ እስራኤል ግዛቶች መፈጸማቸውን ገልጿል።የእስራኤል ጦር ሠራዊት ቃል አቀባይ ለፈረንሳይ ዜና ወኪል ኤኤፍፒ ጥቃቶቹ በሞርታር እንደተፈጸሙ ገልጸዋል።ሐማስ ባለፈው ቅዳሜ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ ግጭቱ ከተባባሰ በኋላ በእስራኤል እና በሶሪያ መካከል የከባድ መሳሪያ ተኩስ ልውውጥ ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው ነው።Article share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 0:200:20በአራት ቀናት ውስጥ ከ260 ሺህ በላይ ፍልስጥኤማውያን ከጋዛ ተፈናቅለዋል፡ የተባበሩት መንግሥታት
Getty ImagesCopyright: Getty Imagesየእስራኤል ጦር ሠራዊት የፍልስጥኤሟን ግዛት ጋዛን በጦር አውሮፕላኖች መደብደቡን በቀጠለበት በአሁኑ ጊዜ ከ260 ሺህ በላይ ሰዎች ከጋዛ መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግሥታት አስታወቀ።ድርጅቱ እንዳለው ይህ በአራት ቀናት ያጋጠመው የነዋሪዎች መፈናቀል ከሰባት ዓመት በፊት ጋዛ ውስጥ ሁለት ወራት ለሚጠጋ ጊዜ ቆይቶ በነበረው ግጭት ከተፈናቀሉት የበለጠ ነው። የተፈናቃዮች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊጨምር እንደሚችል ይጠበቃል።ጋዛ ሰርጥ ውስጥ 2.3 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች የሚኖሩ ሲሆን፣ በጠባብ ስፍራ ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ተጠጋግተው ከሚኖሩባቸው ቦታዎች መካከል የሚጠቀስ ነው።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጨምሮ እንዳለው ለቀናት በቀጠለው የአየር ጥቃት ጋዛ ውስጥ ከአንድ ሺህ በላይ የመኖሪያ ቤቶች ወድመዋል።የእስራኤል የአየር ጥቃት በቀጠለበት ሁኔታ በጋዛ ውስጥ ለሚገኙ ነዋሪዎች መሠረታዊ አቅርቦቶችን ማሟላት “በጣም ፈታኝ” እየሆነ መምጣቱ ተገልጿል።ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በቀጠለው ግጭት እስካሁን በእስራኤል በኩል 1,200 እንዲሁም ከፍልስጥኤም ወገን ደግሞ ከ900 በላይ ሰዎች ተገድለዋል።Article share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 12:31 10 ጥቅምት 202312:31 10 ጥቅምት 2023የዛሬ ዋና ዋና ክስተቶች በአጭሩ
BBCCopyright: BBCባለፈው ቅዳሜ የተቀሰቀሰው የእስራኤል እና የሐማስ ውጊያ ለአራተኛ ቀን ቀጥሎ እስራኤል ጋዛን በጦር ጀቶቿ ስትደበድብ፣ ሐማስ ደግሞ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል መተኮሱን ቀጥሏል።በዛሬው ዕለት የተከሰቱ ቁልፍ ነገሮችን አጭሩ እነሆ፡…
- ·የሐማስ ታጣቂዎች እስራኤላውያን ነዋሪዎች አሽኬሎን ከተባለችው ከተማ ለቀው እንዲወጡ አሰጠንቅቀው አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ የሮኬት ተኩስ በከተማዋ ውስጥ ተሰምቷል።
- ·የሐማስን ጥቃት ተከትሎ የደረሱበት ያልታወቁ የአሜሪካ ዜጎች ዘመዶች በእስራኤሏ መዲና ቴል አቪቭ ውስጥ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እየጠበቋቸው ስላሉት የቤተሰቦቻቸው አሳዛኝ ታሪኮችን ተናግረዋል።
- ·ከቅዳሜ ጀምሮ በእስራኤል የአየር ድብደባዎች የተገደሉ ፍልስጥኤማውያን ቁጥር ወደ 830 ሲደርስ፣ በእስራኤላውያን በኩል የተመዘገበው ሞት ደግሞ ቢያነስ 1,008 መድረሱ ተዘግቧል።
- ·ሐማስ “ውጊያው አስኪቆም ድረስ” በእገታው ስር ስላሉ እስራኤላውያን ጉዳይ እንደማይነጋገር አሳውቋል። አስካሁን ባለ መረጃ ከ100 አስከ 150 የሚደርሱ እስራኤላውያን በሐማስ እገታ ውስጥ እንዳሉ ይታመናል።
- ·እስራኤል ጋዛ ላይ የምትፈጽመው የአየር ጥቃት ቀን ከሌት ሳይል የቀጠለ ሲሆን፣ ሐማስም ሮኬቶቹን ማስወንጨፉን ቀጥሏል።
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- የታተመዉ 8:52 10 ጥቅምት 20238:52 10 ጥቅምት 2023የሳዑዲው ልዑል ሞሐመድ ቢን ሳልማን ለፍልስጥኤማውያን ድጋፋቸውን ገለጹ
ReutersCopyright: Reutersልዑል አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማንImage caption: ልዑል አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማንየሳዑዲው ልዑል አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማን አገራቸው የፍልስጥኤማውያን መብት እንዲከበር ድጋፏን እንደምትቀጥል ተናገሩ።ሳዑዲ አረቢያ መሪ የሆኑት ቢን ሳልማን ይህንን ያሉት እስራኤል በሐማስ የተፈጸመባትን ጥቃት ተከትሎ ጋዛ ውስጥ ከባድ ጥቃት እያካሄደች ባለበት ጊዜ ከፍልስጥኤም ፕሬዝዳንት ማሐሙድ አባስ ጋር በስልክ በተወያዩበት ጊዜ ነው።ቢን ሳልማን “ፍልስጥኤማውያን ተገቢ መብቶቻቸው፣ የተረጋጋ ሕይወት፣ ፍትሃዊ እና ዘላቂ ሰላምን እንዲያገኙ ለማስቻል” አገራቸው ድጋፏን ትቀጥላለች ብለዋል።ጨምረውም ከዓለም አቀፍ እና ከአካባቢያው ማኅበረሰብ ጋር በመሆን ግጭቱ እንዳይስፋፋ እየሰሩ መሆናቸውን ለአባስ ገልጸውላቸዋል።ፍልስጥኤሙ ፕሬዝዳንት ማሐሙድ አባስ እና ጋዛን የተቆጣጠረው ሐማስ የፖለቲካ ተቀናቃኞች ናቸው። አባስ ሌላኛውን የፍልስጥኤም ግዛት ዌስት ባንክን የተቆጣጠረው የፋታህ ንቅናቄ እና የፍልስጥኤም ነጻነት ድርጅት (ፒኤልኦ) መሪ ናቸው።ሳዑዲ አረቢያ ለፍልስጥኤም ያላትን ድጋፍ የገለጸችው በአሜሪካ አማካይነት ከእስራኤል ጋር ያላትን ግንኙነት ለመሻሻል ድርድር እየተደረገ ባለበት ጊዜ ነው።ተንታኞች የተቀሰቀሰው ግጭት ግንኙነታቸውን ለማሻሻል በእስራኤል እና በሳዑዲ መካከል በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት ደቅኗል ብለዋል።ቅዳሜ ዕለት የተፈጸመውን የሐማስን ጥቃት ተከትሎ ሳዑዲ አረቢያ ባወጣችው መግለጫ ለግጭቱ መባባስ እስራኤልን ተጠያቂ አድርጋለች።Article share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 8:15 10 ጥቅምት 20238:15 10 ጥቅምት 2023ውጊያው ሳይቆም በታጋቾች ጉዳይ ላይ አንደራደርም፡ ሐማስ
Getty ImagesCopyright: Getty Imagesውጊያው እስኪያቆም ድረስ በቁጥጥሩ ስር ስላሉ ታጋቾች ሐማስ ከእስራኤል ጋር እንደማይደራደር የቡድኑ ፖለቲካ ቢሮ ኃላፊ ኢስማኤል ሃኒያህ ተናገሩ።“በቁጥጥራችን ስር ያሉ የጠላት አስረኞች ጉዳይ ጦርነቱ ከማብቃቱ በፊት እንደማይነሳ ጥያቄ ላቀረቡልን ወገኖች ሁሉ አሳውቀናቸዋል” ያሉት ሃኒያህ ቡድናቸው “ጉዳዩን የሚቀበለው የሚፈልገውን ምላሽ ሲያገኝ ብቻ ነው” ብለዋል።ሐማስ ባለፈው ቅዳሜ በእስራኤል ላይ ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ፣ ከደቡባዊ እስራኤል አካባቢዎች በ100 እና በ150 መካከል የሚገኙ ሰዎች በፍልስጥኤማዊው ቡድን ቁጥጥር ስር እንደሚገኙ ተዘግቧል።የኳታር እና የአሜሪካ አሸማጋዮች ሐማስ እና እስራኤል በእጃቸው ያሉ ሴቶች እና ሕጻናት እስረኞችን እንዲለዋወጡ ጥረት እያደረጉ መሆናቸውን ሮይርስ ዘግቦ ነበር።የሐማስ ጥቃትን ተከትሎ ለቀናት የቆየ የአጸፋ ጥቃት እየፈጸሙ ያሉት የእስራኤል መከላከያ ኃይሎች ዛሬ ማክሰኞም የሐማስ ናቸው ያሏቸውን ኢላማዎች ማጥቃታቸውን ቀጥለዋል።ሰኞ ሌሊት የእስራኤል አየር ኃይል 200 ኢላማዎችን ጋዛ ውስጥ መደብደቡን ገልጸዋል።Article share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 6:49 10 ጥቅምት 20236:49 10 ጥቅምት 2023ሰበርበጋዛ የተገደሉ ፍልስጥኤማውያን ቁጥር 770 ደረሰ
ReutersCopyright: Reutersእስራኤል በጋዛ ሰርጥ እየፈጸመቻቸው ያሉ የአየር ጥቃቶችን ተከትሎ በጋዛ ሰርጥ የተገደሉ ፍልስጥኤማውያን ቁጥር 770 ደረሰ።በተጨማሪም 4 ሺህ 100 መቁሰላቸውን የእስራኤል ጤና ሚኒስቴር ገልጿል።እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ሙሉ ከበባ እንዲፈጸም ትዕዛዝ መስጠቷን ተከትሎ የዓለም የጤና ድርጅት ለሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት መተላለፊያ እንዲኖር ጥሪ አቅርቧል።እስራኤል በጋዛ የኤሌክትሪክ፣ ምግብ፣ ነዳጅ እና ውሃ አቅርቦት እንዲቋረጥም ማድረጓን ተከትሎ ነው የዓለም የጤና ድርጅት እና ዩኒሴፍ የሰብዓዊ እርዳታ እንዲገባ እየጠየቁ ያሉት።የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኃላፊ ቮልከር ቱርክ የሃማስን ጥቃት አውግዘው የእስራኤል ከበባ በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት ህገወጥ ነው ብለዋል።Article share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 6:49 10 ጥቅምት 20236:49 10 ጥቅምት 2023በእስራኤል እና በሐማስ መካከል የተፈጠረው ግጭት አጀማመር ምን ይመስላል?ቅዳሜ ዕለት በጋዛ የሚገኙ የፍልስጥኤም ታጣቂዎች ጥቃት ፈጽመዋል። ጥቃቱ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ታይቶ የማይታወቅ ነው ተብሏል። ለመሆኑ ለቀናት ቀጥሎ የበርካቶችን ሕይወት የቀጠፈው ግጭት አጀማመር እና ዋና ዋና ጉዳዮች ምን ይመስላሉ?ተጨማሪ ያንብቡArticle share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 6:11 10 ጥቅምት 20236:11 10 ጥቅምት 2023በጋዛ 187 ሺህ ፍልስጥኤማውያን ተፈናቅለዋል- ተመድ
ReutersCopyright: Reutersእስራኤል ገና መጀመሩ እንደሆነ በገለጸችው የጋዛ የአየር ጥቃቶችን ተከትሎ 187 ሺህ ፍልስጥኤማውያን መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታውቋል።ቁጥሩ ከዚህ ሊልቅ እንደሚችልም ነው ተመድ ያሳሰበው።በጋዛ ባሉ 83 የተባበሩት መንግሥታት ትምህርት ቤቶች ውስጥ 137 ሺህ 500 ፍልስጥኤማውያን ተጠልለው ይገኛሉ ተብሏል።በጋዛ የሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት የፍልስጥኤም ስደተኞች ኤጀንሲ ጽህፈት ቤት በአየር ጥቃቱ ጉዳት ደርሶበታል ተብሏል።በጋዛ የሚገኙ የምግብ ማከፋፈያ ማዕከላት በመዘጋታቸው ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ ፍልስጥኤማውያን የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እርዳታ ማግኘት አልቻሉም ተብሏል።እስራኤል ጋዛ ሰርጥን ሙሉ በሙሉ በመዝጋት ከበባ እንዲደረግ አዛለች። በጋዛ ‘ኤሌክትሪክ፣ ምግብ፣ ነዳጅ አይኖርም ሲሉም የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት ትዕዛዝ ሰጥተዋል።ጋዛ ሰርጥ ወደ 2.3 ሚሊዮን የሚጠጉ ፍልስጥኤማውያን መኖሪያ ስትሆን ለ16 ዓመታት ያህል የቆየ ከበባ ውስጥ ትገኛለች።Article share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 5:18 10 ጥቅምት 20235:18 10 ጥቅምት 2023ሐማስ በእስራኤል ላይ ለፈጸመው ጥቃት ምክንያቱ ምንድን ነው?ፍልስጥኤማዊው ታታቂ ቡድን ሐማስ ቅዳሜ መስከረም26/2016 ዓ.ም. በእስራኤል ላይ የፈጸመው ጥቃት በመጠኑ እና ባደረሰው ጉዳት ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ነው። ክስተቱ በድነገት ያጋጠመ ቢሆንም ለአስርታት በፍልስጥኤማውያን እና በእስራኤል መካከል የዘለቀው ውጥረት ውጤት ነው። ሐማስ እንደሚለው ለዚህ ጥቃት በርካታ ምክንያቶች ኣሉት ሲሆን፣ ከእነዚህ መካከል አራቱን እንደመልከት።ተጨማሪ ያንብቡArticle share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 4:27 10 ጥቅምት 20234:27 10 ጥቅምት 2023በእስራኤል የሚገኙ ኤርትራውያን ተጎጂዎችን ለመርዳት አልባሳት እያሰባሰቡ ነውበእስራኤል የሚኖሩ ኤርትራውያን በአገሪቷ ደቡባዊ ክፍል የሚገኙ ተጎጂዎችን ለመርዳት አልባሳት፣ ውሃ እና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን እያሰባሰቡ ነው።ተጨማሪ ያንብቡArticle share tools
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- ይህንን ማስፈንጠሪያ ይውሰዱ
- ያጋሩView more share optionsይህንን ለሰው አጋራ
- የታተመዉ 3:28 10 ጥቅምት 20233:28 10 ጥቅምት 2023የእስራኤል ጦር በጋዛ ድንበር 35 ክፍለ ጦር ማሰማራቱን አስታወቀ
EPACopyright: EPAየእስራኤል መከላከያ ኃይል በጋዛ ሰርጥ ድንበር 35 ክፍለ ጦር ማሰማራቱን አስታውቋል።እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ እየፈጸመቻቸው ካሉ የአየር ጥቃቶች በተጨማሪ በምድር ላይ ከፍተኛ ወታደራዊ ጥቃት በቅርቡ ትጀምራለች ተብሎ ይጠበቃል።“ለወደፊት ለሚደረገው ዘመቻ መንገድ እያመቻቹ መሆናቸውንም” የሰራዊቱ ቃለ አቀባይ ሪቻርድ ሄክት ተናግረዋል።አንድ ክፍለ ጦር በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን ይዟል።የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በጋዛ ላይ እየተፈጸሙ ያሉ የአየር ጥቃቶች ገና እየጀመሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

OREN ROSENFELDCopyright: OREN ROSENFELDበስምምነቱ ከሐማስ ጋር የሚካሄደውን ጦርነት የሚመራ ካቢኔ ተቋቁሟልImage caption: በስምምነቱ ከሐማስ ጋር የሚካሄደውን ጦርነት የሚመራ ካቢኔ ተቋቁሟልየእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ እና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪው ቤኒ ጋንትዝ የአስቸኳይ ጊዜ መንግሥት ለማቋቋም ተስማሙ።ሁለቱ ፖለቲከኞች እዚህ ስምምነት ላይ የደረሱት ሐማስ ድንገተኛ ጥቃት ከፈጸመ በኋላ እስራኤል መጠነ ሰፊ የአጸፋ እርምጃ በጋዛ ላይ እያካሄደች ባለበት አምስተኛ ቀን ላይ ነው።ይህንን ስምምነት ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታኒያሁ፣ ጋንትዝ እና የአገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር ያሉበት “የጦርነት ካቢኔ” ያቋቁማሉ ተብሏል።በስምምነቱ መሠረት ጦርነቱ በሚካሄድበት ጊዜ “የጦርነቱን ሂደት ከሚመለከቱ ጉዳዮች በስተቀር ማንኛውም አይነት ሕግም ሆነ የመንግሥት ሃሳብ ለውሳኔ አይቀርብም።”በተጨማሪም ከዚህ ቀደም ከፍተኛ የመንግሥት ሥልጣንን እንዲይዙ የተሾሙ ሰዎች የኃላፊነት ጊዜ በጦርነቱ ወቅት ሁሉ የሚቀጥል ይሆናል።ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታኒያሁ እና የናሽናል ዩኒቲ ፓርቲ ሊቀ መንበር ጋንትዝ የአስቸኳይ ጊዜ መንግሥት ለማቋቋም የተስማሙት ላለፉት ቀናት ንግግር ካደረጉ በኋላ ነው።ከስምምነቱ በኋላ ከሁለቱም ወገን በጋራ በወጣ መግለጫ ላይ “የአስቸኳይ ጊዜ መንግሥት ለመመሥረት እና ጦርነቱን የሚመራ ካቢኔ ለማቋቋም ተስማምተዋል።“ጦርነቱን የሚመራው ካቢኔም ጠቅላይ ሚኒስትሩን፣ የመከላከያ ሚኒስትሩን እና የተቃዋሚ ፓርቲውን መሪ በአባልነት ይዞ ይመሠረታል” ተብሏል።ከሦስቱ ባለሥልጣናት በተጨማሪ የጦርነቱ መሪ ካቢኔን በታዛቢነት የሚያገለግሉ ሁለት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ይካተቱበታል።Article share tools
Getty ImagesCopyright: Getty Imagesየጋዛ ዋነኛ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ማዕከልImage caption: የጋዛ ዋነኛ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ማዕከልእስራኤል በሐማስ ለተፈጸመባት ጥቃት አጸፋ ጋዛ ላይ ከበባ በመጣል ለአምስተኛ ቀን ተከታታይ የአየር ጥቃት እየፈጸመች ሲሆን፣ ሐማስም የሮኬት ጥቃቱን ቀጥሏል።በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የጋዛ ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል።መሠረታዊ አቅርቦቶች በከተማዋ ውስጥ እየተሟጠጡ መሆናቸው እየተዘገበ ነው።ዛሬ ረቡዕ እስካሁን የተከሰቱ ዋና ዋና ጉዳዮች ምንድን ናቸው?
BBCCopyright: BBCባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ የተቀሰቀሰውን ግጭት በተመለከተ የዓለም አገራት የተለያየ አቋማቸውን እያንጸባረቁ ነው።በዚህም በግልጽ ከእስራኤል ወይም ከፍልስጥኤም ጎን መሠለፋቸውን ያሳወቁ አገራት የመኖራቸውን ያህል፣ ከየትኛውም ወገን ሳይቆሙ ገለልተኛ አቋም ያንጸባረቁም አሉ።ከ54ቱ የአፍሪካ አገራት መካከልም ከፍልስጥኤም ጎን የተሰለፉ፣ እስራኤልን የደገፉ፣ ገለልተኛ አቋም የያዙ እና ለጊዜው ዝምታን የመረጡ አገራት አሉ።በዚህ ዝርዝር አስካሁን በይፋ አቋማቸውን ያንጸባረቁ የአፍሪካ አገራት ተካተዋል።Article share tools
EPACopyright: EPAእስራኤል ጋዛ ላይ እያካሄደችው ባለው የአየር ጥቃት ምክንያት የተገደሉ እና ጉዳት የደረሰባቸው ፍልስጥኤማውያን ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ነው።የፍልስጥኤም የጤና ሚኒስቴር ረቡዕ እኩለ ቀን ላይ ባወጣው መረጃ የተገደሉ ሰዎች አሃዝ 1,055 ሲደርስ፣ ከ5,100 በላይ ሰዎች ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጨምሮ እንዳለው፣ በጥቃቱ ከተጎዱት ሰዎች መካከል 60 በመቶዎቹ ሴቶች እና ሕጻናት ናቸው።ሐማስ ቅዳሜ ዕለት በፈጸመው ጥቃት የተገደሉ እስራኤላውያን 1,200 ሲሆኑ ከ2,700 በላይ የሚሆኑ ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።Article share tools
Getty ImagesCopyright: Getty Imagesየእስራኤል አየር ኃይል ጋዛ ውስጥ የሐማስ ናቸው ያላቸውን ኢላማዎች ለአራተኛ ቀን እየደበደበ ባለበት በዛሬው ዕለት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የእስራኤል ወታደሮች ከጋዛ አቅራቢያ ሰፍረዋል።የሐማስ ጠንካራ ይዞታ በሆነችው ጋዛ ላይ እየተፈጸመ ባለው የአየር ጥቃት ምክንያት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የጋዛ ነዋሪዎች መፈናቀላቸው የተዘገበ ሲሆን፣ በነዳጅ ችግር ምክንያት በከተማዋ በሰዓታት ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ይቋረጣል።የሐማስ ተዋጊዎችን ለማደን እና የታገቱ ዜጎቿን ለማስለቀቅ እስራኤል እግረኛ ሠራዊቷን ወደ ጋዛ ታሰማራ እንደሆነ አስካሁን የታወቀ ነገር ባይኖርም፣ አስፈላጊውን ሁሉ እርምጃ እንደምትወስድ አስታውቃለች።የእስራኤል ጦር ሠራዊት ዛሬ ረቡዕ እንዳሳወቀው በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮቹ “የተሰጣቸውን ተልዕኮ ለመፈጸም ዝግጁ ሆነው” ከጋዛ አቅራቢያ ይገኛሉ ብሏል።Article share tools
Getty ImagesCopyright: Getty Imagesየእስራኤልን ጥቃት በመቃወም ዌስት ባንክ ራማላህ ውስጥ ሰልፍ የወጡ ፍስጥኤማውያንImage caption: የእስራኤልን ጥቃት በመቃወም ዌስት ባንክ ራማላህ ውስጥ ሰልፍ የወጡ ፍስጥኤማውያንዛሬ ረቡዕ ማለዳ ጎህ ሲቀድ ከጋዛ ባሻገር በወረራ በተያዘችው ዌስት ባንክ ውስጥ ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጥኤማውያን እስራኤል በጋዛ ላይ እየፈጸመችው ያለውን የአውሮፕላን ድብደባ በመቃወም ሰልፍ አድርገዋል።የፍልስጥኤም ዜና አገልግሎት እንደዘገበው ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ የፍልስጥኤምን ሰንደቅ ዓላማ እና በጥቃቱ የተገደሉ ሰዎችን ፎቶፍራፎች ይዘው ነው አደባባይ የወጡት።Article share tools
Getty ImagesCopyright: Getty Images
Getty ImagesCopyright: Getty Imagesየእስራኤል ጦር ሠራዊት የፍልስጥኤሟን ግዛት ጋዛን በጦር አውሮፕላኖች መደብደቡን በቀጠለበት በአሁኑ ጊዜ ከ260 ሺህ በላይ ሰዎች ከጋዛ መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግሥታት አስታወቀ።ድርጅቱ እንዳለው ይህ በአራት ቀናት ያጋጠመው የነዋሪዎች መፈናቀል ከሰባት ዓመት በፊት ጋዛ ውስጥ ሁለት ወራት ለሚጠጋ ጊዜ ቆይቶ በነበረው ግጭት ከተፈናቀሉት የበለጠ ነው። የተፈናቃዮች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊጨምር እንደሚችል ይጠበቃል።ጋዛ ሰርጥ ውስጥ 2.3 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች የሚኖሩ ሲሆን፣ በጠባብ ስፍራ ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ተጠጋግተው ከሚኖሩባቸው ቦታዎች መካከል የሚጠቀስ ነው።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጨምሮ እንዳለው ለቀናት በቀጠለው የአየር ጥቃት ጋዛ ውስጥ ከአንድ ሺህ በላይ የመኖሪያ ቤቶች ወድመዋል።የእስራኤል የአየር ጥቃት በቀጠለበት ሁኔታ በጋዛ ውስጥ ለሚገኙ ነዋሪዎች መሠረታዊ አቅርቦቶችን ማሟላት “በጣም ፈታኝ” እየሆነ መምጣቱ ተገልጿል።ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በቀጠለው ግጭት እስካሁን በእስራኤል በኩል 1,200 እንዲሁም ከፍልስጥኤም ወገን ደግሞ ከ900 በላይ ሰዎች ተገድለዋል።Article share tools
BBCCopyright: BBCባለፈው ቅዳሜ የተቀሰቀሰው የእስራኤል እና የሐማስ ውጊያ ለአራተኛ ቀን ቀጥሎ እስራኤል ጋዛን በጦር ጀቶቿ ስትደበድብ፣ ሐማስ ደግሞ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል መተኮሱን ቀጥሏል።በዛሬው ዕለት የተከሰቱ ቁልፍ ነገሮችን አጭሩ እነሆ፡…
ReutersCopyright: Reutersልዑል አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማንImage caption: ልዑል አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማንየሳዑዲው ልዑል አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማን አገራቸው የፍልስጥኤማውያን መብት እንዲከበር ድጋፏን እንደምትቀጥል ተናገሩ።ሳዑዲ አረቢያ መሪ የሆኑት ቢን ሳልማን ይህንን ያሉት እስራኤል በሐማስ የተፈጸመባትን ጥቃት ተከትሎ ጋዛ ውስጥ ከባድ ጥቃት እያካሄደች ባለበት ጊዜ ከፍልስጥኤም ፕሬዝዳንት ማሐሙድ አባስ ጋር በስልክ በተወያዩበት ጊዜ ነው።ቢን ሳልማን “ፍልስጥኤማውያን ተገቢ መብቶቻቸው፣ የተረጋጋ ሕይወት፣ ፍትሃዊ እና ዘላቂ ሰላምን እንዲያገኙ ለማስቻል” አገራቸው ድጋፏን ትቀጥላለች ብለዋል።ጨምረውም ከዓለም አቀፍ እና ከአካባቢያው ማኅበረሰብ ጋር በመሆን ግጭቱ እንዳይስፋፋ እየሰሩ መሆናቸውን ለአባስ ገልጸውላቸዋል።ፍልስጥኤሙ ፕሬዝዳንት ማሐሙድ አባስ እና ጋዛን የተቆጣጠረው ሐማስ የፖለቲካ ተቀናቃኞች ናቸው። አባስ ሌላኛውን የፍልስጥኤም ግዛት ዌስት ባንክን የተቆጣጠረው የፋታህ ንቅናቄ እና የፍልስጥኤም ነጻነት ድርጅት (ፒኤልኦ) መሪ ናቸው።ሳዑዲ አረቢያ ለፍልስጥኤም ያላትን ድጋፍ የገለጸችው በአሜሪካ አማካይነት ከእስራኤል ጋር ያላትን ግንኙነት ለመሻሻል ድርድር እየተደረገ ባለበት ጊዜ ነው።ተንታኞች የተቀሰቀሰው ግጭት ግንኙነታቸውን ለማሻሻል በእስራኤል እና በሳዑዲ መካከል በሚደረገው ጥረት ላይ እንቅፋት ደቅኗል ብለዋል።ቅዳሜ ዕለት የተፈጸመውን የሐማስን ጥቃት ተከትሎ ሳዑዲ አረቢያ ባወጣችው መግለጫ ለግጭቱ መባባስ እስራኤልን ተጠያቂ አድርጋለች።Article share tools
Getty ImagesCopyright: Getty Imagesውጊያው እስኪያቆም ድረስ በቁጥጥሩ ስር ስላሉ ታጋቾች ሐማስ ከእስራኤል ጋር እንደማይደራደር የቡድኑ ፖለቲካ ቢሮ ኃላፊ ኢስማኤል ሃኒያህ ተናገሩ።“በቁጥጥራችን ስር ያሉ የጠላት አስረኞች ጉዳይ ጦርነቱ ከማብቃቱ በፊት እንደማይነሳ ጥያቄ ላቀረቡልን ወገኖች ሁሉ አሳውቀናቸዋል” ያሉት ሃኒያህ ቡድናቸው “ጉዳዩን የሚቀበለው የሚፈልገውን ምላሽ ሲያገኝ ብቻ ነው” ብለዋል።ሐማስ ባለፈው ቅዳሜ በእስራኤል ላይ ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ፣ ከደቡባዊ እስራኤል አካባቢዎች በ100 እና በ150 መካከል የሚገኙ ሰዎች በፍልስጥኤማዊው ቡድን ቁጥጥር ስር እንደሚገኙ ተዘግቧል።የኳታር እና የአሜሪካ አሸማጋዮች ሐማስ እና እስራኤል በእጃቸው ያሉ ሴቶች እና ሕጻናት እስረኞችን እንዲለዋወጡ ጥረት እያደረጉ መሆናቸውን ሮይርስ ዘግቦ ነበር።የሐማስ ጥቃትን ተከትሎ ለቀናት የቆየ የአጸፋ ጥቃት እየፈጸሙ ያሉት የእስራኤል መከላከያ ኃይሎች ዛሬ ማክሰኞም የሐማስ ናቸው ያሏቸውን ኢላማዎች ማጥቃታቸውን ቀጥለዋል።ሰኞ ሌሊት የእስራኤል አየር ኃይል 200 ኢላማዎችን ጋዛ ውስጥ መደብደቡን ገልጸዋል።Article share tools
ReutersCopyright: Reutersእስራኤል በጋዛ ሰርጥ እየፈጸመቻቸው ያሉ የአየር ጥቃቶችን ተከትሎ በጋዛ ሰርጥ የተገደሉ ፍልስጥኤማውያን ቁጥር 770 ደረሰ።በተጨማሪም 4 ሺህ 100 መቁሰላቸውን የእስራኤል ጤና ሚኒስቴር ገልጿል።እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ሙሉ ከበባ እንዲፈጸም ትዕዛዝ መስጠቷን ተከትሎ የዓለም የጤና ድርጅት ለሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት መተላለፊያ እንዲኖር ጥሪ አቅርቧል።እስራኤል በጋዛ የኤሌክትሪክ፣ ምግብ፣ ነዳጅ እና ውሃ አቅርቦት እንዲቋረጥም ማድረጓን ተከትሎ ነው የዓለም የጤና ድርጅት እና ዩኒሴፍ የሰብዓዊ እርዳታ እንዲገባ እየጠየቁ ያሉት።የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኃላፊ ቮልከር ቱርክ የሃማስን ጥቃት አውግዘው የእስራኤል ከበባ በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት ህገወጥ ነው ብለዋል።Article share tools
ReutersCopyright: Reutersእስራኤል ገና መጀመሩ እንደሆነ በገለጸችው የጋዛ የአየር ጥቃቶችን ተከትሎ 187 ሺህ ፍልስጥኤማውያን መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታውቋል።ቁጥሩ ከዚህ ሊልቅ እንደሚችልም ነው ተመድ ያሳሰበው።በጋዛ ባሉ 83 የተባበሩት መንግሥታት ትምህርት ቤቶች ውስጥ 137 ሺህ 500 ፍልስጥኤማውያን ተጠልለው ይገኛሉ ተብሏል።በጋዛ የሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት የፍልስጥኤም ስደተኞች ኤጀንሲ ጽህፈት ቤት በአየር ጥቃቱ ጉዳት ደርሶበታል ተብሏል።በጋዛ የሚገኙ የምግብ ማከፋፈያ ማዕከላት በመዘጋታቸው ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ ፍልስጥኤማውያን የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እርዳታ ማግኘት አልቻሉም ተብሏል።እስራኤል ጋዛ ሰርጥን ሙሉ በሙሉ በመዝጋት ከበባ እንዲደረግ አዛለች። በጋዛ ‘ኤሌክትሪክ፣ ምግብ፣ ነዳጅ አይኖርም ሲሉም የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት ትዕዛዝ ሰጥተዋል።ጋዛ ሰርጥ ወደ 2.3 ሚሊዮን የሚጠጉ ፍልስጥኤማውያን መኖሪያ ስትሆን ለ16 ዓመታት ያህል የቆየ ከበባ ውስጥ ትገኛለች።Article share tools
EPACopyright: EPAየእስራኤል መከላከያ ኃይል በጋዛ ሰርጥ ድንበር 35 ክፍለ ጦር ማሰማራቱን አስታውቋል።እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ እየፈጸመቻቸው ካሉ የአየር ጥቃቶች በተጨማሪ በምድር ላይ ከፍተኛ ወታደራዊ ጥቃት በቅርቡ ትጀምራለች ተብሎ ይጠበቃል።“ለወደፊት ለሚደረገው ዘመቻ መንገድ እያመቻቹ መሆናቸውንም” የሰራዊቱ ቃለ አቀባይ ሪቻርድ ሄክት ተናግረዋል።አንድ ክፍለ ጦር በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን ይዟል።የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በጋዛ ላይ እየተፈጸሙ ያሉ የአየር ጥቃቶች ገና እየጀመሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል።