October 24, 2023 

Konjit Sitotaw 

ፕሮፌሰር ገቢሳ ኤጀታ የአሜሪካን ብሄራዊ የሳይንስ ሜዳሊያ ሽልማትን ከፕሬዚደንት ጆ ባይደን እጅ ዛሬ ተቀብለዋል።

በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ዘርፍ እጅግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላደረጉ የአሜሪካ ዜጎች በሚሰጠው በዚህ ሽልማት 19 ሰዎች የተካተቱ ሲሆን የፐርዱ ዩኒቨርሲቲ ባልደረባው ፕሮፌሰር ጋቢሳ አንዱ ሆነዋል።

መምህርና ተመራማሪው ፕሮፌሰር ጋቢሳ ኤጄታ ለሽልማቱ ያበቃቸው በከፍተኛ የምርምር ስራቸው የእፅዋት ዘረመል ምህንድስና በመጠቀም በረሃማ የአየር ንብረት እና ነፍሳትን የሚቋቋሙ የአዝርዕት ዘሮችን በማግኘታቸው ነው። ግኝታቸው በሚሊዮን ለሚቆጠሩ የምግብ ዋስትናን እንደሚያረጋግጥ ታምኖበታል።

ፕሮፌሰር ጋቢሳ ኤጄታ በምግብ ዘርፍ ላበረከቱት አስተዋፅዖ ከዚህ በፊት ከዓለም የምግብ ፕሮግራሙ ሽልማት የተበረከተላቸው መሆኑ የሚታወቅ ነው።

Via White House/EPA By Elias Meseret