
ከ 7 ሰአት በፊት
የደቡብ አፍሪካ ፓርላማ ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት የማይልኩ ወላጆችን ዘብጥያ እንዲወርዱ የሚፈቅድ ሕግ አረቀቀ።
ደቡብ አፍሪካ ያረቀቀችው አዲሱ የትምህርት ሕግ አንድ ተማሪ ትምህርት ቢያቋርጥ ወይም ተማሪው ዕድሜው ለትምህርት ደርሶ ትምህርት ቤት ካልገባ ወላጆች እስከ 12 ወራት በእስር እንዲቀጡ ያዛል።
ይህ አዲሱ ሕግ በትምህርት ቤቶች አካላዊ ቅጣቶችንም ይከለክላል።
ረቂቅ ሕጉ በአገሪቱ ፓርላማ አባላት በ223 ድጋፍ እና 83 ተቃውሞ ጸድቋል።
ደቡብ አፍሪካን እያስተዳደረው የሚገኘው አፍሪካን ናሽናል ኮንግረስ (ኤኤንሲ) ፓርቲ “ሕጉ አሁናዊ እና ታሪካዊ ፈተናዎችን በመሻር የትምህርት ስርዓቱን ያዘምናል” ብሏል።
ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲ ዴሞክራቲክ አሊያንስ ግን ፓርላማው ያጸደቀውን ሕግ ተችቷል።
እንደ ፓርቲው ከሆነ ይህ የሕግ አዋጅ መንግሥት በትምህርት ቤቶች ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር እንዲኖሩት አድርጎ የትምህርት ሰርዓት እንዲወድቅ ሊያደርግ ይችላል ሲል ስጋቱን ገልጿል።
- በአሜሪካ 18 ሰዎች በመግደል ሲፈለግ የነበረው ሞቶ መገኘቱ ተገለጸከ 7 ሰአት በፊት
- “ስኬታማ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የምሆን ይመስለኛል…” አኖልድ ሽዋዝኒገርከ 8 ሰአት በፊት
- ቤተ-እስራኤላዊው አቨራ መንግሥቱ እና ለዓመታት በሐማስ እገታ ሥር ያሉ ሌሎች እስራኤላውያንከ 8 ሰአት በፊት
የትምህርት ባለሙያዎች የደቡብ አፍሪካ የትምህርት ስርዓት ቀውስ ውስጥ ነው ያለው ይላሉ።
በደቡብ አፍሪካ ትምህርት የሚያቋርጡ ተማሪዎች ቁጥር ትንሽ የሚባል አይደለም።
የአገሪቱ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ በ2022 ባወጣው አሃዝ ላይ ዕድሜያቸው 15 ዓመት ከሆናቸው ተማሪዎች 3 በመቶ እንዲሁም ዕድሜያቸው 17 ከሆኑ 9 በመቶ ያክሉ እአአ 2021 ላይ ትምህርት አቋርጠዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ሪዲንግ ሊትረሲ ስተዲ ዓለም አቀፍ ተቋም በሰራው ጥናት ለማንበብ የሚቸገሩ በርካታ ተማሪዎች ከሚገኙባቸው አገራት መካከል አንዷ ደቡብ አፍሪካ መሆኗን አሳይቶ ነበር።
በዚህ ዓመት የተደረገ ጥናት ዕድሜያቸው 10 ከሆኑ 10 ደቡብ አፍሪካውያን ተማሪዎች 8 ያክሉ ለማንበብ ይቸገራሉ።