Tesfaye Woldesilassie   

· ጄነራሎችና የዘረፋ ቡድኖችና መዋቅሮች

1ኛ:- ጄነራል ጌታቸው ጉዲና ፡ የመከላከያ መረጃ ዋና መምሪያ ነው።

በዋናነት በመከላከያ ወስጥ ከተደራጁ የተለያዩ የዝርፊያ ቡድኖች መሃል የአንዱ መሪ ነው፤

*በአደንዛዥ እጽና በሌሎችም ሱሶች የተጠመደ፣ ታይላንድና ዱባይ ለህክምና ካልተመላለሰ እድሜው ሊያጥር የሚችል፣ የጤንነቱ ጉዳይ እንኳን አሳስቦት የሌቦች ቁንጮነቱን አሳልፎ ሌሎች ለመሰጠት ፈቃደኛ ያልሆነ፣ ሰው ነው።

* ጄነራሉ ዋናው የገቢው ምንጭ በማእድን ዙሪያ በከተማ ልማት ስራዎች ላይ ኢንቨስት ለማደረግ የሚፈልጉ የውጭ ዜጎች በቀላሉ ፈቃድ እና መሬት እንዲያገኙ በማድረግ ከፈተኛ ገቢ የሚያገኝ የድለላ ስራ የሚሰራ ነው።

*የድለላ ስራው የቡድን አባላት ጄነራል ባጫ ደበሌ ኬንያ እንዲሁም ብርሃኑ ጸጋዬ የጅቡቲ አምባሳደሮች፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታዋ ብርቱካን፣ የከተማና የልማት ሚኒስቴር ጫልቱ ሳኒ ናቸው።

*ጀኔራል ባጫ ደበሌ እና አንባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ በሳምንት ሁለት ቀን፣ ማክሰኞ እና ቅዳሜ በኤምባሲው ወጪ በርቱካን እውቅና አዲስ አበባ እየተመላለሱ ጉዳይ እንዲያስፈጽሙ ተፈቅዶላቸዋል፣

* ጄኔራል ባጫ ደበሌ ከጅቡቲው አምባሳደር ብርሀኑ ፀጋየ እና ከቀድሞው ማአድን ሚኒስተር ታከለ ኡማ ጋር በመቀናጀት የባቡር ትራንስፖርቱንና አየር መንገዱን በመጠቀም ከአገር የሚያስወጡትን ከፍተኛ የመአድን፣ ወርቅና የሀገር ቅርሶችን በመሸጥ በሚያገኙት የውጭ ምንዛሪ በዱባይ፣ በካናዳ፣ በቻይና እና በእንግሊዝ የተቀናጡ ቤቶችና አፓርትመንቶች ንግድ ላይ ተሰማርተዋል፣ በተጨማሪ ሁለቱም የተሰጣቸውን የአምባሳደርነት ሀላፊነት በመጠቀም ኤምባሲዎቻቸውን የግል የማአድናት መጋዘን በማድረግ እየተገለገሉባቸው ነው።

* ጄነራል ጌታቸው፣ ከድለላ ስራው ባሻገር የማዕድናት የሲሚንቶ፣ የእርሻ እንዲሁም የመንግሥታዊ ሃብቶች ዝርፊያ ቡድን አጠቃላይ አዛዥ ነው፡፡

* ይሄ ጄነራል ሚንስቴሮችን፣ የክልል አመራሮችን፣ አምባሳደሮችን ፣የደህንት አመራሮችን እና ያደራጃቸውን ነጋዴወች በጥንቃቄ በተደራጀ ሠንሠለት ይመራል፡፡

* በአማራ ክልል የሚደረገውን ጦርነት እንዲጀመር በወታደራዊ ካውንስሉ ውስጥ ከፍተኛ ግፊት ሲያደርግ የነበረ ሰው ነው፡፡

2ኛ:- ሌ/ጄነራል ይልማ መርዳሣ፤ ይህ ጄነራል የዚህ ዝርፊያ ቡድን ም/አዛዥ ሲሆን በመላ ሃገሪቱ የሚሰበሰቡ ማዕድናትን ከአየር ምድብ በሚንቀሳቀሡሱ ሄሊኮፕተሮች ፣ አንቶኖቮች ማዕድናትን ወደ ደብረዘይት የሚያስጭን እና በአሁኑ ሰዓት አንድ የጭነት አውሮፕላን ከአየር መንገድ ለዚሁ ዓላማ እንዲውል አመቻችቷል፡፡

* በእዚህ ጄነራል ስር የተደራጁ የቡድን አባላትአሉ፣ የግምሩክ ኮሚሽነሩ ደበሌ ካበታ፣ ሌንጮ ባቲ የሳኡዲ አማባሳደር፣ ናቸው።

3ኛ:- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ:- እንደማእረጉ የሌቦች የአዛዥነት ስልጣን የሌለውም፣ ሆኖም የእሱ ስራ ወደ ውጭ ሃገራት በሚያደርጋቸው ይፋዊ ይሁኑም የሚስጥራዊ ጉዞዎችም በቡድኑ የሚቀርብለትን ውድ የሆኑ ማዕድናት አብረውት ተጭነው ይወጣሉ የማሻሻጥ ስራ ይሰራል።

በብርሃኑ ጁላ ቡድን ስር የተሰባሰቡ ጅቦች አሉ ፣

ሺመልስ አብዲሳ ፣

አዳነች አበቤ፣

አቤ ሳኖ የንግድ ባንክ ዋና ስራአስኪያጅአባዱላ ገመዳ

የአብይ አህመደ የቀርብ ወዳጅና አማካሪ፣ ቀንያ ያደታ በአዲስ አበባ ከተማ የመሬት አስተዳደር ሹም ቀድሞ የመከላከያ ሚኒስቴር የነበረ ፣

አሻድሊ ሃሰን ናቸው።

ይህ ቡድን ገፋፊው በሚል ስም ይታወቃል። በህንዶችና በቻያናዎችና በሃገር በቀል ኮንታራክተሮች ስም የተከፈቱ ትልልቅ የኮንስትራክሽን ኩባንያዎች አሏቸው። የሀገሪቱን ትልልቅ ፕሮጀከቶች ተቋራጮች እየሆኑ የለምንም ጨረታ ይወስዳሉ። የቤተመንግስቱ ስራዎች አነስተኛ ግድቦች፣ መኖሪያና ንግድ ቤቶች ግ ንባታ ላይ በበረትና በስሚንቶ ንግድ ላይ ተሰማርተዋል። በከተማው ውስጥ የሚፈልጉትን የትኛውንም ቦታ ኗሪውን በቀላሉ በማፈናቀል መውሰድ የሚችሉ ናቸው።

የእዚህ ቡድን ሌላው አባል ሌ/ጂነራል አስራት ዲኒሮ ሲሆን ይህ ግለሰብ ለቤንሻንጉል አማጽያን መሳሪያ ሲሸጥ እጅ ከፍንጅ ተይዞ የብርሃኑ ጁላን ሚስጥር ያውቃል በሚል ማለሳለሻ ተጠያቂ ሳይሆን የቀረ ነው። ቡድኑ እንደ ጄነራል አበባው ቡድን ባይሆንም በጎን መሳሪያ ይነግዳል።

ይህ የጄነራሎች የማፊያ ቡድን፣ ባለንበት ወቅት የጦሩ አዛዥ የሆነው ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከስልጣኑ ተነስቶ በምትኩ ሌ/ጄነራል ብርሃኑ በቀለ እንዲሾም ተግቶ እየሰራ ይገኛል።

4ኛ ጄኔራል አበባው ታደሰ ዋና የስራ ድርሻ የጦር መሳሪያ ሽያጭ ነው፣ የቡድኑ አባላት፣

ሌ/ጂነራል መሃመድ ተሰማ፣

ሌ/ጄነራል ሰልሞን ይተፋ፣

ሌ/ጄንራል ሃጫሉ ሸልመ

ሌ/ጄነራል ጥጋቡ ይልማ ናቸው፣

* ይህ ቡድን ለደቡብ ሱዳን፣ እንዲሁም ለሱዳን ተፋላሚዎች እና ለአልሸባብ ሳይቀር መሳሪያ የሚሸጥ ቡድን ነው።

*እነዚህ ጄነራሎች በሁሉም ክልሎች በስፋት መሬት በመውሰድ የሚታወቁ ናቸው።

5ኛ ሜ/ጀነራል ተስፋዬ አያሌው አለሙ፣

ከኢጋዱ ወርቅነህ ገበየሁ እንዲሁም ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ጋር በመሆን አደገኛ የውንብድና ስራ ይሰራሉ።

የባቡር መንገዱን አስተዳደሮችና ጥበቃ አባላትን ለነሱ በሚያመቹ ሰዎች አደራጅተዋል። በሃገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የውጭ ምንዛሪ የጥቁር ገበያ በመቆጣጠር ፣የተለያዩ የውጭ ምንዛሪዎችን ከአገር በማውጣት የውጭ ምንዛሬ ግሽበት በማሳደግ ዋኛዎቹ ተዋኛኖች ናቸው።

* ከእዚህ በተጨማሪ ኮኬንና ሌሎችንም አደገኛ የአደንዛዝ እፆችን፣በመድሀኒትና ቁጥጥር ባለስልጣን ወደሀገር እንዳይገቡ የተከለከሉ መድሀኒቶችንና የተለያዩ የህክምና ግብአቶችን መኪናና የመኪና መለዋወጫወችን በባቡር ትራንስፓርቱ በስፋት ወደሃገር ውስጥ በማስገባት በከፍተኛ ደረጃ ህገወጥና አደጋኛ ንግድ ላይ ተሰማርተዋል።

6ኛ ሌ/ጄነራል አብደራሃማን እሥማኤል የመከላከያ የሎጀስቲክ ስራ ዋና መምሪያ ሲሆን፣ የቡድኑ የሎጀስቲክ አንቀሳቃሽ እና በመከላከያ የሚገዙ የተባሉ ወደ ሃገር ውስጥ የሚገቡ ዕቃወች ሳይቀር በመከላከያ ስም እንዲገቡ የሚያደርግ እና የቡድኑን አጠቃላይ የሎጀስቲካዊ ሥራወችን የሚያቀላጥፍ ሰው ነው።

የመከላከያ ግዥወችን በእዚሁ ቡድን ዙሪያ ባሉ ነጋዴወች ብቻ እንዲቀርብ በማድረግ የሃገር ሃብትን በመዝረፍና በማዘረፍ ስራ ላይ የተሰማራ ወሮበላ ነው።

7ኛ:- ሌ/ጄነራል ብርሃኑ በቀለ፤ የሰሜን ምዕራብ እዝ አዛዥ ነው።

በዋናነት ለዚህ ቡድን የፓለቲካ ሥጋት የሆነውን የሰሜን እና የአማራ ክልል አካባቢ ያለውን አጠቃላይ ፓለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዲመታ እና ከሱዳን ጄነራሎች ጋር የሚደረጉ የጥቅም ትስስሮችን የሚመራ የቡድኑ አባል ነው፡፡

8ኛ:- ሌ/ጄነራል ሹማ አብደታ የልዩ ዘመቻ ዕዝ አዛዥ፤

በሲዳማ እና ሻኪሶ አካባቢ ያሉ የወርቅ፣ የኦፓል እና ሌሎች የከበሩ ማዕድናት ከቀጠናው በግል መኪኖቻቸው እንዲሰበሰቡ በማድረግ በኩንታል እየጫኑ ወደ አዲስ አበባ የሚያደርስ እና በነጄነራል ባጫ ደበሌ አመቻችነት ወደ ኬንያ የሚልክ፡፡ በተጨማሪም የቡድኑ የመቺ ክንፍ አባል የሆነ፡፡

9ኛ:- ብ/ጄነራል ደረጀ መገርሣ ፡፡

የመከላከያ ፋውንዴሽን ሃላፊ ነው።፣

የቡድኑ አባል እና በተለይም ጄነራሎች በውጭ ሃገራት፣ የሪል እስቴት ግዥ እና በሃገር ውስጥ በኦሮሚያ፣ ደቡብ፣ ጋምቤላ እና አፋር የጄነራሎቹን የእርሻ ኢንቨስተመንት የሚያስተባብርና የሚቆጣጠር፣ የዘረፋ ሠንሠለት የሚዘረጋ ሰው ነው፡፡

10ኛ:-ብ/ጄነራል ሠይፈ አንጊ

አሶሳ አካባቢ የሚገኝ የቤንሻንጉልን የወርቅ ዝርፊያ እያደራጀ ለቡድኑ የሚያቀርብ እና ቤንሻንጉል ክልልን በበላይነት የሚቆጣጠር ነው። ከክልል አመራሮች መሃል የዘረፋ ተባባሪዎች መልምሎ የጄነራሎቹን ቡድን ስራ የሚያስፈጽም ወንበዴ ነው።

11ኛ:-ብ/ጄነራል አብድሮ ከድር፤የሪፓብሊኩ ጥበቃ አዛዥ ሲሆን፣ አዲስ አበባ ውስጥ በዚሁ ቡድን ትዕዛዝ የሚደረጉ አፈናወችን በተለይም የቡድኑን ሚሥጢር ያውቃሉ የተባሉትን ያሚያስወግድ እና ኦፕሬሽኑን የሚመራ፣ በአዲስ አበባ የመሬት ነክ እና ኢንቨስትመንት ጉዳዮችን የሚያስፈጽም፤ ከፌደራል ፓሊስ አዛዥ፣ ኮሚሸነር ደመላሽ ጋር ወዳጅነት የነበረው፣ በቅርቡ ግን ከጥቅም ጋር በተያያዘ ከኮሚሽነሩ ጋር ከባድ ግጭት ውስጥ የገባ ግልሰብ ነው፡፡

ዛሬ በሀገሪቱ አሉ የተባሉ ሚዲያዎች ሲያስተላልፉለት የነበረው

የሰራዊቱ ቁመና ምን ይመስላል በአጭሩ

ይህ በአደባባይ ሮኬትና ሚሳይል ሰድሮ ትርኢት የሚያሳየው እንኳን በሰው ልጆች፣ በአማልክት ጦረኞች የማይፈታ የሚመስለው ጦር ቁመና ደግሞ ከዘረፋው የባሰ ጉድ የሚታይበት ነው። በትንሹ ብቻ ጨለፍ አድርጌ ልንገራችሁ።

1ኛ፤ ከላይ የተዘረዘሩት ጀነራሎች የሚግባቡ የሚዋደዱ ለስራ የሚመካከሩ ሳይሆን ደረጃ በሙስና የበከቱ ከፍተኛ አመራሮች ለጎሪጥ የሚተያዩ ጥቅም ያስተሳሰራቸው ናቸው።እርስ በርሱ የማይተማመን፣ የጎሪጥ የሚተያይ፣ እጅግ አጸያፊ በሆኑ ቃላት እርስ በርስ የሚዘላለፍ፣ ክፍለ ጦር በዘር የሚመለምሉ ናቸው፣ ሰራዊቱ እርስ በርሱ እንዳይተማመን ሆን ብሎ የሚሰራ አመራር ያለው ሰራዊት ነው።

እነዚህ ሌቦች ምንም አይነት ወታደራዊ ስነምግባር በሌላቸው አዛዦች የሚመራ ሰራዊት፣ ሞራሉ የላሸቀ፣ በሃገሩና በሰራዊቱ ተስፋ ይቆረጠ ነው።

ከሃምሌ 18 2015 እስከ መስከረም 7 2016 ባለው ጊዜ ብቻ የኦሮሚያና የአማራ ክልልን ሳይጨምር ከሰራዊቱ መሳሪያውን ይዞ የከዳው ወታደር ቁጥር አስራ ስድስት ሸህ አራት መቶ አስራ ሶስት፣ 16413፣ ነው።

ይህ ቁጥር ውጊያ እየተደረገበት ያለውን የአማራ ክልል አይጨምርም።

ፍልሰቱ አስጨናቂ ስለሆነበት ነው አብይ በየቦታው እየዞረ የሚያስመርቅ ።

በነገራችን ላይ ይህ ከደሃው ቤተሰብ የሚመለመሉ የኢትዮጵያ ልጆች በሰራዊቱ ህይወታቸው ተስፋ የሚቆርጡት ገና በስልጠና ላይ እያሉ ነው። በጦር ካምፕ ውስጥ ለስልጠና ያስገቧቸውን ወጣቶች በረሃብ የሚይሳገርፉ ናቸው።

አዋሽ አርባ ማስልጠኛ ለታንክና ለፓትሮል ሹፍርና ስልጠና የገቡ ወታደሮች በረሃብ አለቅን በሚል ባለፈው ሳምንት እሮብ እለት ሰልፍ ያደረጉ ሲሆን፣ ብር ሸለቆ ማስልጠኛ የሚገኙ ወታደሮች ባለፈው ቅዳሜ በተመሳሳይ ምግብና የልብስ አቅርቦት አተሟላልንም በማለት ሰልፍ አድርገዋል። በስልጠና ወቅት ምስኪን ምልምሎችን በረሃብ መቅጣት የተለመደ እየሆነ መጥቷል።ጀነራሎቹ በዝርፊያ አውሮፓ እና አሜሪካ ቤት ይገዛሉ።

116ኛው የኢትዮጵያ መከላከያ በአል በሚል ስም የሚከበረው በአል እንዲህ አይነት እድፍ በውስጡ ተሸክሞ ነው ።