ቱርክን ወደ ኦቶማን ዘመን ዝናዋ ለመመለስ የሚጥሩት ኤርዶዋን ምን እያደረጉ ነው?

7 ህዳር 2023
ቱርክ ከኦቶማን ግዛተ መንግሥት መውደቅ በኋላ እንደ አገረ መንግሥት የተመሰረተችበትን 100ኛ ዓመት እያከበረች ነው።
የቱርክ አባት በመባል የሚታወቁት አታቱርክ፣ አገራቸውን ከሃይማኖት ገለልተኛ እና ዘመናዊ እሳቤን እንድትላበስ መሠረት ጥለዋል።
በዘመናዊው ዓለም መድረክ ጉልህ ተጽዕኖ ያላቸው የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶዋን እንደ ኦቶማን ዘመን ሁሉ ቱርክን በዓለም ኃያል ለማድረግ እየጣሩ ነው። ይሳካላቸው ይሆን?