
Saturday, 23 December 2023 20:47
Written by Administrator

በጉብኝቱ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ኢንጅነር) ስለኢንስቲትዩቱ ሥራዎች ገለጻ አድርገዋል፡፡ በውይይቱ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂን ለማልማት በኢንስቲትዩቱ የሚሰሩ የምርምር ተግባራት ለሀገር የሚበጁ መሆናቸውን እንደተገነዘቡ ተመራማሪዉ ተናግረዋል።
ሳይንቲስቱ የሰዉሰራሽ አስተዉሎት ቴክኖሎጂ ለሰዉ ልጅ የሚያበረክተውን ሚና እንዲሁም በጠፈር ምርምር የቴክኖሎጂዉ አበርክቶ ጉልህ መሆኑን ገልፀዋል።
የሰዉሰራሽ አስተዉሎት ቴክኖሎጂ ቸግር ፈቺ የምርምር ዘርፍ በመሆኑ ወጣቶቸና በውጪ የሚኖሩ የዲያስፖራ አባላት በንቃት አንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።
ብርሃኑ ቡልቻ (ዶ/ር) በጨረቃ ላይ ዉሃ መኖር አለመኖሩን የሚመረምር መሳሪያ የፈጠሩ የናሳ ተመራማሪ ናቸዉ።