December 29, 2023 – ነቢዩ ሲራክ 

የማለዳ ወግ …

” እባካችሁ ልጆቻችን ተውልን “

=====================

* ልጆቻችን ነጭ አምላኪ ሳይሆን ፈጣሪን ፈርተው እንዲያድጉ ፍቀዱልን

የትምህርት ሚኒስትር በአቡነ ጎርጎሪዮስ ተማሪዎች በትምህርት ወቅት መንፈሳዊ መዝሙር እንዳይዘምሩ እገዳ መጣሉን ሰምተናል ። ምንም ማድረግ ባይችሉም በርካታ ወላጆች ልጆቻችን ነጭ አምላኪ ሳይሆን ፈጣሪን ፈርተው እንዲያድጉ ፍቀዱልን ” በሚል በውሳኔው ላይ ከፍ ያለ ተቃውሞ እና ቅሬታቸውን በተለያየ መንገድ እየገለጹ ይገኛሉ ።

እኔም እላለሁ…

==========

በህዝብ የመንግስት ት/ቤቶች የማለዳ ትምህርት መጀመሪያ ሰዓት ከኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር ውጭ በመዝሙር ወይም በጸሎት ዱአ በህብረት መዘመር አግባብ አይደለም ቢባል ልስማማ እችል ይሆናል ። ነገር ግን እንደ አዎሊያና አቡነ ጎርጎሪዎስ ባሉ የእምነት ተቋማት ስር በግል የሚተዳደሩ ት/ቤት ተማሪዎች መዝሙር አትዘምሩ ብሎ እገዳ መጣል አግባብነቱ ለእኔም አልገባኝምና እነሆ አጠይቃለሁ …

* ” የጥበብን መጀመሪያ ፈጣሪን መፍራት ነው” እናም ልጆቻችን በእምነት ተቋማት ስር በሚተዳደሩ ት/ቤቶች ልጆቻችኝ ክርትያኑም በመዝሙር ፣ ሙስሊም በዱአ ጸሎት እና ምስጋና ትምህርት የመጀመራቸው ጉዳት ምኑ ላይ ነው ⁉️

* ሀገራችን በረከሰ የግብረ-ሰዶማውያን መስፋፋት እየናወጠች ዝም ተብሎ ልጆቻችን ኢትዮጵያዊነት ሥነ-ምግባር ታንጸው ፤ ፈጣን በመፍራት በግብረ – ገብነት ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ፣ በእውቀት ጎልብተው ፣ ታሪክና የባህል ውርሳቸውን አክብረው ቢማሩ ምን አለበት ⁉️

* ከስር መሰረቱ በግብረ- ገብነት ኮትኩቶ ልጆቻችን ማሳደግ የወላጅ ደጋፊ ፣ ሀገር ፣ ወገን አክባሪ፣ ልማትና እድገት የሚሰሩ በአዳዲስ እሳቤዎች መፍለቂያ ምንጭ እንዲሆኑ ማገዝ አይደለምን ⁉️

* ታዳጊ ልጆችዎ የነገ ህልማቸውን የሚያልሙትን ምህዳርን ማስፋት ፣ በስልጡኑ አለም የተሳሳተ ስነ ልቦና ተጠልፈው ከስጋና ነፍስ ስብራት እንዳይጎዱ መታደግ አይደለምን ⁉️

* ልጆቻችን በራሳቸው ማንነት እንዲኮሩ በልሳነ ግዕዝን ማስተማር ይጠቅማል ብየ አምናለሁ ። ከእምነት ውጭ እንደ ቀደምት ቋንቋ ግዕዝ እንደ ትምህርት የመማራቸው ጥቅሙ በቀደሙ አባቶቹ የተላለፉ መጻሕፍት እና ድርሳናትን ትውልዱ በራሱ መንገድ ተጉዞ አለምን እንዲመረምር እገዛ አያደርግም ትላላችሁ ⁉️

እባካችሁ ልጆቻችን ነጭ አምላኪ ሳይሆን ፈጣሪን ፈርተው እንዲያድጉ ፍቀዱልን … ልጆቻችን ተውልን ‼️

ነቢዩ ሲራክ

ታህሳስ 17 ቀን 2016 ዓም