በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በቾ ወርዳ አዋሸ ቡኔ ቀበሌ ከትላንት በስቲያ ከሌሊቱ 5:00 ሰዓት ላይ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት አራት ሰዎች እንደተገደሉ ታውቋል።
በጥቃቱ 28 የጭነት ተሽከርካሪዎች ተቃጥለው ከጥቅም ውጭ መሆናቸውንም ምንጮች ተናግረዋል።
ታጣቂዎቹ ጥቃቱን የፈጸሙት ተሽከርካሪዎቹ ከወሊሶ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ ሳሉ መኾኑን የገለጡት ምንጮች፣ ተሽከርካሪዎቹን አስቁመው ቤንዚን አርከፍከፈው እንዳቃጠሏቸው ገልጸዋል።
ታጣቂዎቹ ተሽከርካሪዎችን ካቃጠሉና አራቱን ሰዎች ከገደሉ በኋላ፣ በርካታ ሰዎችን አፍነው እንደወሰዱና ሌሎች ደሞ ከአካባቢው በመሸሽ ሕይወታቸውን እንዳተረፉ ሉማወቅ ተችሏል።
ዋዜማ