January 6, 2024 – Getachew Shiferaw

ይህ ሰው የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ሰራተኛ ነው። የኦሮሞ ብልፅግና በተለይም የአብይን መልዕክት ሲያሰራጭ ነው የሚውለው። የአዲሱ አረጋ የቅርብ ሰው መሆኑ ተገልፆአል። ሌሎቹ ጋር አብሮ እንደሚውል በፎቶ ይታያል።
ይህ የኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ሰራተኛ ታዲያ ኦርቶዶክሶች ከኦሮሚያ መፅዳት አለባቸው ብሎ በይፋ ፅፏል። ይህ ሰው በጥንቃቄ ሊሰራ ይችላል ተብሎ የሚታሰበው የክሙኒኬሽን መስሪያ ቤት ሰራተኛ ሆኖ ነው የዘር ፍጅትን በግልፅ የሚሰብከው። የኮሙኒኬሽን መስሪያ ቤቱ ላይ በዚህ ልክ ከተቀሰቀሰ ሌሎቹ ምን እንደሚያደርጉ ማሰብ ቀላል ነው። https://t.me/GetachewShiferaw/7327?single
የዚህ ሰው ቅስቀሳ ያረጋገጠው የዘር ፍጅቱ የሚፈፀመው በኦሮሚያ መዋቅር መሆኑን ነው። አውርተው፣ አሰማርተው የሚያስፈጁትን ለምደውትና አማራና ኦርቶዶክስን መፍጀት ህጋዊና ግዴታ አድርገውት በይፋ ይፃፋል። የፃፈው ከአለቆቹ የተነገረውን ነው። የፃፈው በመዋቅር የሚሰሩትን ነው!
አቡነ ሉቃስ አብይን ተቹ ብለው ህዝብ ላይ የዘር ፍጅት ያውጃሉ። የአቡነ ሉቃስ አጀንዳ ህዝብን ለመፍጀት ሰበብ ነው! በይፋ ህዝብን ከኦሮሚያ እናፀዳለን ብለው እየፃፉ ነው። ኦሮሚያ መዋቅሩ የሚያምነው ይህን ነው! እስካሁን የተፈፀመው ወንጀል እንዲህ በመዋቅር ተቀስቅሶ የተፈፀመ ስለመሆኑ ይህ አንድ ማስረጃ ነው! https://t.me/GetachewShiferaw/7327?single