
January 12, 2024 – Getachew Shiferaw
በአብይ አህመድ ትዕዛዝ ነው!
አብይ አህመድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ላይ በያዘው በውጭ ኃይሎች የተደገፈ ፕሮጀክት ለማስፈፀም ከመረጣቸው ስልቶች አንደኛው ቤተ ክርስቲያንን መሪ ማሳጣት ነው። ባለፈው ቤተ ክርስቲያን ላይ በሞከረው ጥቃት ጠንከር ካሉበት አባቶች አንዱ አቡነ ጴጥሮስ ናቸው።
ሰሞኑን ጥምቀትን ለማክበር ወደ ሀገረ ስብከታቸው እንደሚሄዱ ሲታወቅ ገና አውሮፕላኑ ሳይነሳ በሄዱበት ቀሩ ብለው የሀሰት መረጃ አሰራጩ። ወዲያው ገና ያልተሰራጨ መፅሐፋቸውን በዘመድኩን በቀለ ስም የታተመ አስመስለው በኢንተርኔት ለቀቁት። የሚያሸማቅቋቸው መስሏቸው ነው።
ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው በአብይ አህመድ ቀጥታ ትዕዛዝ ነው። እንዳይመለሱ ለማድረግ ነው። ቤተ ክርስቲያኗን መሪ አልባ አስቀርቶ አብይ አህመድ በፕሮጀክት አስፈፃሚነት የያዘውን ኦርቶዶክስን ማመንፈቅ ማስፈፀሚያ መንገድ ነው። አይሆንም! (ጌታቸው ሽፈራው )
