January 30, 2024 – Konjit Sitotaw
በአዲስ አበባ የመሬት አገልግሎቶች ታገዱ።
በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የመዋቅራዊ አደረጃጀት ጥናት ተከናውኖ በአዳስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ጸድቆ ወደ ተግባር እንዲገባ የተወሰነውን ውሳኔ መሰረት በማድረግ የሠራተኞች የባህሪ እና የቴክኒክ ፈተና ተሰጥቶ ውጤቱ ይፋ መደረጉ ይታወቃል።
በዚህም አዲስ በተጠናው መዋቅራዊ አደረጃጀት ጥናት መሰረት የሰራተኞች ድልድል ተሰርቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ከዛሬ ጥር 21 /2016 ዓ.ም ጀምሮ የመሬት አገልግሎቶች በጊዜያዊነት መታገዳቸውን የአዲስ አበባ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።