ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ከማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች ጋር በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ሁኔታ ላይ ተወያዩ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዛሬ የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም ከማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች ጋር በወቅታዊ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሁኔታና ቀጣይ የቤት ሥራዎች ላይ ተወያይተዋል።
በውይይቱ የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም ፣ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይን ጨምሮ የሥራ አመራር ጉባኤ አባላት ተገኝተዋል።
©ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት
