May 1, 2024 – Konjit Sitotaw 

አፍሪካ ኅብረት፣ ከኹለት ሳምንት በፊት በግቢው ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ለግንባታና ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ በሚል በተጭበረበሩ ሰነዶች ሊወጣ የነበረው ገንዘብ 6 ሚሊዮን ዶላር እንደነበር ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጧል።

ኅብረቱ የተደረገበትን የማጭበርበር ሙከራ የፋይናንስ ሠራተኞቹ ማክሸፋቸውን ገልጦ፣ ሙከራው ግን በከፍተኛ አንክሮ የምመለከተው ክስተት ነው ብሏል። ኅብረቱ፣ የማጭበርበር ሙከራው በደኅንነት ሥርዓቱ ላይ ፍተሻ ለማድረግ በር እንደከፈተለትም ጠቅሷል።

በባንክ ሒሳቡ ላይ ወደፊት የማጭበርበር ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ ለመከላከል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በትብብር እየሠራ መኾኑንም ኅብረቱ አስታውቋል።