ዝንቅ ‹‹ሄቦ›› የየም የዘመን መለወጫ

በጋዜጣዉ ሪፓርተር

ቀን: September 22, 2024

ሄቦ ከጭጋግና ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከአሮጌው ወደ አዲሱ ምዕራፍ መሻገሪያ የም ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል ነው፡፡ በዓሉ የአዲስ ዓመት መባቻ በመሆኑ በተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ ተወላጆች ከወላጆቻቸው ጋር የሚገናኙበት እንደሆነ ይነገራል፡፡ የዘንድሮው የሄቦ በዓል መስከረም 20 እና 21 ቀን 2017 ዓ.ም. በዞኑ ዋና ከተማ ሳጃ እንደሚከበር የየም ዞን የባህልና ቱሪዝም መሥሪያ ቤት አስታውቋል፡፡