Wednesday, 02 October 2024 16:01

Written by  Administrator

ዶ/ር እመቤት መለሰ  የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ

በቅርቡ የንብ ባንክ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሹመው የነበሩት ዶ/ር እመቤት መለሰ፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ሆነው መሾማቸው ተሰምቷል።

የገንዘብ ሚኒስቴር መስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም  በፃፈው  ደብዳቤ ላይ እንደተገለጸው፤ ዶ/ር እመቤት መለሰ  ከጥቅምት 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ  ፕሬዚዳንት ሆነው ተሹመዋል።

ዶ/ር እመቤት፣ የልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ከመሆናቸውም በፊት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስትራቴጂ ፕላኒንግና ትራንስፎርሜሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው ማገልገላቸው ይታወቃል፡፡

የፖሊሲ ባንኩን ላለፉት 4 ዓመታት በፕሬዚዳንትነት ሲመሩ የነበሩት ዶ/ር ዮሐንስ አያለዉ  በግል ምክንያት ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ካስታወቁ በኋላ፣ የአማራ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነዉ በቅርቡ መሾማቸው ይታወሳል።