
Tuesday, 08 October 2024 16:21
Written by Administrator
በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ላይ ጭማሪ መደረጉ ተገለጸ። በዚህም መሰረት የቤንዚን ዋጋ በሊትር 91 ብር ከ14 ሳንቲም መግባቱ ነው የተገለጸው።
የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ባሰራጨው ደብዳቤ እንዳመለከተው፣ የዋጋ ጭማሪ የተደረገው በዓለም ገበያ የታየውን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ላይ በመመስረት ነው። ይኼው የነዳጅ ምርቶች ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ ከዛሬ መስከረም 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ በስራ ላይ እንደሚውል ተጠቅሷል።
የቤንዚን ዋጋ 91 ብር ከ14 ሳንቲም በሊትር ሲሆን፤ ነጭ ናፍጣ 90 ብር ከ28 ሳንቲም በሊትር፤ ኬሮሲን 90 ብር ከ28 ሳንቲም በሊትር፤ ቀላል ጥቁር ናፍጣ 100 ብር ከ20 ሳንቲም በሊትር፤ ከባድ ጥቁር ናፍጣ 97 ብር ከ67 ሳንቲም በሊትር እና የአይሮፕላን ነዳጅ በሊትር 77 ብር ከ76 ሳንቲም እንደሆነ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባሰራጨው መረጃ ተጠቁሟል።