October 19, 2024 – VOA Amharic
መሪውን ያህያ ሲንዋርን በመግደል በሐማስ ላይ ከባድ ጉዳት ያደረሰችው እስራኤል ታጣቂውን ቡድን ለመደምሰስ ላለፈው አንድ ዓመት የያዘችውን ጥቃት ዛሬ አርብም ገፍታበታለች።
የያህያ ሲንዋርን መገደል በማድነቅ የተናገሩት የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ እአአ ጥቅምት ሰባት ሀማስ የቀሰቀሰው ጦርነት አላበቃም ብለው በማስከተል ግን የመጨረሻው መጀመሪያ ነው ብለዋል።