October 24, 2024 – VOA Amharic
የሶማሊያ መንግሥት እአአ በሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ ላይ በሀገሯ ሥራ እንዲጀምር ለታቀደው የአፍሪካ ኅብረት አረጋጊ ተልእኮ (አውሶም) ወታደር የሚያዋጡ ሀገሮችን እንደሚመርጥ አረጋግጧል።
የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ረቡዕ ባወጣው መግለጫ ሶማሊያ የተልእኮውን አቅጣጫ “ትኩረቱን በግልጽ ሉዓላዊነት ላይ” ባደረገ መንገድ ትመራዋለች ብሏል፡፡