October 29, 2024 – VOA Amharic
በሱዳን የፍጥኖ ደራሽ ኃይሉ ባደረሰው ጥቃት በአንድ ከተማ ብቻ ከ120 በላይ ሰዎች ሳይገደሉ እንዳልቀረ አንድ የሐኪሞች ቡድን እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታውቀዋል።
ኃይሉ በመካከለኛው ምሥራቅ ሱዳን የነበረውን የበላይነት በሱዳን ሠራዊት መነጠቁን ተከትሎ ለተከታታይ ቀናት በሲቪሎች ላይ ተኩስ መክፈቱን እንዲሁም ሴቶችን እና ልጃገረዶችን አስገድዶ መድፈሩን ተመድ አስታውቋል።