ካማላ ሃሪስ, ዴሞክራት

ካማላ ሃሪስዴሞክራት

ዶናልድ ትራምፕሪፐብሊካን

ለማሸነፍ የሚያስፈልገው 270

223 279

66,443,509 ድምጽ(47.4%)

71,491,756 ድምጽ(51%)

የቀጥታ መረጃ ዶናልድ ትራምፕ, ሪፐብሊካን

https://www.bbc.com/ws/includes/include/vjafwest/1365-2024-us-presidential-election-banner/amharic/app

ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲመረጡ ፣ ሪፐብሊካኖች በሁለቱም ምክር ቤቶች የበላይነት እየያዙ ነው

የትራምፕ ደጋፊዎች
የምስሉ መግለጫ,የትራምፕ ደጋፊዎች

ከ 7 ሰአት በፊት

ዶናልድ ትራምፕ 47ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል።

የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤት የሪፐብሊካን ፓርቲ ዕጩ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ማሸነፋቸውን አሳይቷል።

ትራምፕ ወሳኝ የሆኑትን ግዛቶች ላይ የበላይነት በማግኘት የዲሞክራቶቹ ዕጩ ካማላ ሃሪስን በሰፊ ልዩነት በመምራት ፕሬዝዳንት ለመሆን የሚያስፈልጋቸውን የ270 ኤሌክቶራል ድምጽ አግኝተዋል።

ሪፐብሊካኖች ድላቸውን ይፋ ለማድረግ ሽር ጉድ እያሉ ሲሆን ዶናልድ ትራምፕም የአሸናፊነታቸውን ንግግር አድርገዋል።

ንግግር ለማድረግ እየተዘጋጁ ያሉት ትራምፕ
የምስሉ መግለጫ,ንግግር ለማድረግ እየተዘጋጁ ያሉት ትራምፕ

አሜሪካውያን ፕሬዝዳንታቸውን ለመምረጥ ከሰጡት ድምጽ በተጨማሪ ለሕግ መወሰኛው ምክር ቤት (ሴኔት) እና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ኮንግረስ) አባልነት ለሚወከሉ ሰዎች ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

በዚህም መሠረት በሴኔቱ ውስጥ ሪፐብሊካኖች የበላይነትን ለማግኘት ችለዋል። ባለፉት አራት ዓመታት በዲሞክራቶች የበላይነት ተይዞ የነበረው የሕግ መሰኛው ምክር ቤት አሁን ሪፐብሊካኖች አብላጫውን እንዳገኙበት የወጣው ውጤት ያሳያል።https://flo.uri.sh/visualisation/20078266/embed?auto=1

እስካሁን በታወቁት የምርጫ ውጤቶች እና በሂደቱ ላይ በመመሥረት በተሰጡ ግምቶች ሪፐብሊካኖች ድል እየቀናቸው ይመስላል። ትራምፕ ፕሬዝዳንት ለመሆን ጥቂት ኤሌክቶራል ድምጽ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን፣ ካማላ ወደ ኋላ ቀርተዋል።

በኮንግረሱ ውስጥም ሪፐብሊካኖች ከዲሞክራቶች የበለጠ መቀመጫ አግኝተዋል። ይህ መጪዎቹ አራት ዓመታት በአሜሪካ ሁለቱም ምክር ቤቶች ውስጥ ሪፐብሊካኖች የበላይነት መያዛቸው ዕውን እየሆነ ይመስላል።https://flo.uri.sh/visualisation/20078381/embed?auto=1