November 6, 2024 – VOA Amharic
ዘመናዊ የግብርና ዘዴ እና የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖን መግታት ረሃብን ለማጥፋት ቁልፍ እንደሆኑ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ።
ጠቅላይ ምኒስትሩ አዲስ አበባ ለሶስት ቀናት በሚቆየው “ከረሃብ ነጻ ዓለም” በተሰኘ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ በዓለም የሚታየውን የምግብ ችግር ለመቅረፍ ፈጠራ የታከለበት መፍትሄ እንደሚያሻም ጠቁመዋል።