November 24, 2024 – VOA Amharic
የሱዳን ጦር ላለፉት አምስት ወራት በፈጥኖ ደራሹ ጦር ቁጥጥር ሥር የነበረችውና ከካርቱም በስተደቡብ የምትገኘውን ቁልፏን የሴናር ክፍለ ግዛት ዋና ከተማ ሲንጃን ትላንት ቅዳሜ መቆጣጠሩን አስታወቀ፡፡
ሲንጃ ለ19 ወራት በዘለቀው ጦርነት የምስራቅ እና መካከለኛው ሱዳን አካባቢዎችን በሚያገናኝ ቁልፍ መንገድ ላይ የምትገኝ ስትራቴጅካዊ ከተማ ናት።