November 26, 2024 – VOA Amharic
የዩናይትድ ስቴትስ የግብርና ኢንዱስትሪ ተቋማት፣ ተመራጩ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በህገወጥ መንገድ የገቡ ስደተኞችን ለማባረር የገቡት ቃል በግብርና ዘርፉ በተሰማሩ ሠራተኞች ላይ ተፈፃሚ እንዳይሆን ጠየቁ። ተቋማቱ ይህን የጠየቁት፣ ውሳኔው ህጋዊ ፈቃድ በሌላቸው ስደተኞች ሥራ ላይ በከፍተኛ ደረጃ የሚመረኮዘውን የምግብ አቅርቦት ሰንሰለት ሊያናጋው እንደሚችል በመግለፅ ነው።