November 30, 2024 – VOA Amharic
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በዩክሬን ዋና ከተማ፣ ኪየቭ የሚገኙትን “የውሳኔ መሰጫ ማዕከላት” ኦርሸኒክ በተሰኙ፣ ከድምፅ የፈጠኑ የሩሲያ ተውዘግዛጊ ሚሳኤሎች እንደሚመቱ ትላንት ዝተዋል። ፑቲን ይህን የተናገሩት በዩክሬን የኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት በማድረስ በመላ አገሪቱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ለሚኾኑ ሰዎች ኃይል ካቋረጡ በኋላ ነው፡፡