November 30, 2024 – VOA Amharic
ኢራን ፎርዶ እና ናታንዝ በተባሉ የኑክሌር ማብላያ ጣቢያዎች በሺሕዎች የሚቆጠሩ የተሻሻሉ የኑክሌር ማብላያዎችን በመጠቀም ዩራኒየም ማበልጸግ ልትጀምር መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኑክሌር ተቆጣጣሪ አካል እንዳለው በጦር መሳርያ ደረጃ ዩራኒየም ማምረቷ፣ በቴህራን የኑክሌር መርሃ ግብር ምክንያት እየታየ ያለውን ውጥረት ያባብሳዋል።