December 2, 2024 

የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደኣ በዋስትና እንዲለቀቁ ተወሰነ

የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር ደኤታ አቶ ታዬ ደንደኣ በዋስትና እንዲለቀቁ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት መወሰኑ ተገለጸ፡፡

ዛሬ በዋለው ችሎት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አቶ ታዬ በዋስትና እንዲፈቱ መወሰኑን ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።

በዚህም መሰረት የቅርብ ቤተሰባቸው እንዲለቀቁ የሚያስፈልጉ ሂደቶችኝ በማስፈጸም ላይ እንደሆኑም ነው የተነገረው።