December 5, 2024 – VOA Amharic
ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በዋስ እንዲፈቱ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ከእስር ቤት ሲወጡ በድጋሚ ተይዘው የነበሩት፣የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር ድኤታ አቶ ታዬ ደንደአ ዛሬ ሐሙስ ኅዳር 26 ቀን 2017 ዓ.ም እኩለ ቀን ላይ ፣ ከእስር ተፈተው ከቤተሰቦቻቸው ጋራ መቀላቀላቸውን ባለቤታቸው ወይዘሮ ስንታየኹ አለማየኹ ለአሜርካ ድምጽ ተናግረዋል።