
29 ታህሳስ 2024
በሲዳማ ክልል ቦና ወረዳ አሑድ ዕለት በደረሰ የትራፊክ አደጋ ምክንያት ቢያንስ 71 ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን የክልሉን ፖሊስ ኮሚሽን ዋቢ አድርገው እንደዘገቡት አደጋው የደረሰው አይሱዙ የተባለው የጭነት መኪና በርካታ ሰዎችን አሳፍሮ በመሄድ ላይ ሳለ ነው።
መኪናው ለሰርግ የሚጓዙ ሰዎችን አሳፍሮ ጋላና ተብሎ የሚጠራ ወንዝ አካባቢ ያለ መንገድ ስቶ ወደ ወንዙ መግባቱ ተነግሯል።
ኮሚሽኑ እስካሁን ቢያንስ የ71 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ተናግረው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በአካባቢው ወደሚገኝ ሆስፒታል መወሰዳቸውን ገልፀዋል።
የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች እና የአካባቢው ነዋሪዎች በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች እያፈላለጉ እና ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች እየረዱ እንደሆነ ኮሚሽነሩ አክለዋል።
- በደቡብ ኮሪያ የአውሮፕላን አደጋ 179 ሰዎች ሲሞቱ 2 ሰዎች ተረፉ29 ታህሳስ 2024
- የግብፁ ፕሬዝደንት የኢትዮጵያ እና ሶማሊያን ስምምነት “በቅርበት እየተከታተሉ” እንደሆነ ተናገሩ29 ታህሳስ 2024
- በአሜሪካ መኖሪያ ቤት የሌላቸው እና ጎዳና የሚያድሩ ሰዎች ቁጥር 770 ሺህ ደረሰ29 ታህሳስ 2024
በዚህ ዜና ላይ ተጨማሪ መረጃዎችን እየተከታተልን የምናደርስ ይሆናል።