December 31, 2024 – VOA Amharic
ሩሲያ የጋዝ አቅርቦቷን ከነገ ጀምሮ እንደምታቋርጥ በማስታወቋ፣ በኃይል እጥረት ስጋት የገባት ሞልዶቫ በከባዱ ክረምት ለሚኖረው የማሞቂያና የመብራት ችግር እየተዘጋጀች ነው፡፡
ለአውሮፓ ኅብረት አባልነት በታጨችው ሞልዶቫ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጠው ንብረትነቱ የሩሲያ መንግሥት የሆነው ጋዝፕሮም ሀገሪቱ የ709 ሚሊዮን ዶላር ውዝፍ የመብራት ዕዳ አለባት በማለቱ ነው፡፡