January 6, 2025 – Konjit Sitotaw 

የአእላፋት ዝማሬ የምስጋና መርሐ ግብር  በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናንን በተገኙበት በድምቀት ተካሂዷል

ለሁለተኛ ግዜ የተዘጋጀው የአእላፋት ዝማሬ የምስጋና መርሐ ግብር በቦሌ ደብረ ሳሌም መድሃኒዓለም ካቴድራል በድምቀት ተካሂዷል።

በመርሐ ግብሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ እና ሌሎች ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲሁም ምእመናን ተገኝተዋል፡፡

የጃንደረባው ትውልድ ማኅበር ባዘጋጀው የአእላፋት ዝማሬ የምስጋና መርሐ ግብር ላይ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ምዕመናንና ምዕመናት ተሳትፈዋል።