የአሜሪካ ጦር በፈጸመው የአየር ጥቃት 10 የአል ሻባብ አባላት መገደላቸውን የሶማሊያ መንግሥት አስታውቋል።
የሶማሊያ የማስታወቂያ ሚኒስቴር በመግለጫው እንዳለው፣ የአየር ጥቃቱ የተፈጸመው ቢርሃኒ በተባለና ከኪሲማዮ ሰሜን ምዕራብ 60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ሥፍራ ነው። የሚኒስቴሩ መግለጫ የወጣው ትላንት እሑድ ሲኾን፣ የአየር ጥቃቱ መቼ እንደተፈጸመ ግን አላሳወቀም።
የአሜሪካ ጦር በፈጸመው የአየር ጥቃት 10 የአል ሻባብ አባላት መገደላቸውን የሶማሊያ መንግሥት አስታውቋል።
የሶማሊያ የማስታወቂያ ሚኒስቴር በመግለጫው እንዳለው፣ የአየር ጥቃቱ የተፈጸመው ቢርሃኒ በተባለና ከኪሲማዮ ሰሜን ምዕራብ 60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ሥፍራ ነው። የሚኒስቴሩ መግለጫ የወጣው ትላንት እሑድ ሲኾን፣ የአየር ጥቃቱ መቼ እንደተፈጸመ ግን አላሳወቀም።