January 10, 2025 – VOA Amharic
ከፍልስጤም የነፃነት ድርጅት (ፒ ኤል ኦ) ተወካዮች ጋራ ዛሬ የተገናኙት የግብጹ የውጪ ጉዳይ ምኒስትር የፍልስጤማውያን ራስ ገዝ አስተዳደር እንዲጠናከርና ፍልስጤማውያን በአንድነት እንዲቆሙ ጥሪ አድርገዋል።
በውይይቱ ወቅት የውጪ ጉዳይ ምኒስትር ባድር አብደላቲ ለፍልስጤማውያን ራስ ገዝ አስተዳደር ሃገራቸው ያላትን ድጋፍ እንደገለጹ ከቢሯቸው የወጣው መግለጫ አመልክቷል።
በተጨማሪም ፍልስጤማ