January 14, 2025 – VOA Amharic
ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ ወደ አዋሽ ከተማ ሲቃረብ ሐዲዱን ስቶ በመገልበጥ ቁጥሩ ከ418 የሚበልጥ ሕይወት የጠፋበት የባቡር አደጋ የደረሰው ከአርባ ዓመታት በፊት በ1977 ዓ.ም. በዛሬው ዕለት ነበር፡፡ የፈረንሳይ እና ኢትዮጵያ የባቡር መስመር ኩባኒያን ጠቅሶ አሶሲየትድ ፕሬስ በዕለቱ ያስነበበው ዘገባ እንዳተተው በአደጋው ከሞቱት በተጨማሪ 559 ሰዎች ቆስለዋል፡፡