#ቤዛ ምንድን ነው?

የቃሉ ትርጉም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እና በሌላ ቦታ ሲጠቀስ ተመሳሳይ የማይሆንበት እድል ሰፊ ነው።

🔷የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማህበር በ፮ኛ እትም መዝገበ ቃላቱ ላይ “ቤዛ” የሚለውን ቃል የተረጎመው “የተያዘን ወይም የተወሰደን ነገር ለማስመለስ የሚከፈል ዋጋ፣ ካሣ፣ ለውጥ” በማለት ነው።

ማህበሩ በምሳሌነት የጠቀሳቸውም፦

√ ገንዘብ የህይወት ቤዛ ነው፤ ምሳ ፲፫፣፰

√ የእስራኤል ህዝብ መሬታቸውን ወይም

ቤታቸውን ከሸጡ በኋላ ለመቤዠት ይችሉ ነበር፤

ዘሌ ፳፭፣፳፬-፴፬

√ ኢየሱስ ለሚያምኑበት ሁሉ በሞቱ ቤዛ

ሆነላቸው፤ ማር ፲፣፵፭፤ ኤፌ ፩፣፯፤ ፩ጢሞ

፪፣፭-፮

√ ለሰው የተደረገለት ቤዛነት የሚፈጸመው

ከሙታን ትንሣኤ በኋላ ነው፤ ሮም ፰፣፳፫ ኤፌ

፬፣፴

የሚሉትን ነው።

ስለዚህ ይህ ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥም አንድ ዓይነት ትርጉም ብቻ እንዳለው ማሰብ ከባድ ነው።

👉በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በዚህ ቃል ከተነገሩ ምሳሌዎች ውስጥ የሚከተሉት ጭምር ይገኙበታል፦

🛑እኔ የእስራኤል ቅዱስ አምላክኽ እግዚአብሔር መድኀኒትኽ ነኝ። ግብጽን ለአንተ #ቤዛ አድርጌ፥ ኢትዮጵያንና ሳባንም ለአንተ ፋንታ ሰጥቻለኹ። ኢሳ ፵፫፣፫

🛑በኀይላቸው የሚታመኑ፥ በባለጠግነታቸውም ብዛት የሚመኩ፤ ወንድም ወንድሙን አያድንም፥ ሰውም አያድንም፤#ቤዛውን ለእግዚአብሔር አይሰጥም። (መዝ ፵፰ ፮-፯)

🛑#ቤዛ የላቸውምና፥ እግዚአብሔርንም አልፈሩትምና (መዝ ፶፬፣፲፱)

🛑ለሰው ነፍስ #ቤዛው ሀብቱ ነው። ምሳ ፲፫፣፰

🛑ኃጥእየጻድቅ #ቤዛ ነው፤ በደለኛም የቅን ሰው #ቤዛ ነው። ምሳ ፳፩፣፲፰

🛑ከእነርሱ ሰው ዅሉ እንደ ቍጥራቸው መጠንየነፍሱን #ቤዛ ለእግዚአብሔር ይስጥ። ዘጸአት ፴፣፲፪

🛑የዘለዓለምን #ቤዛነት አግኝቶ አንድ ጊዜ ፈጽሞ ወደ ቅድስት በገዛ ደሙ ገባ እንጂ በፍየሎችና በጥጃዎች ደም አይደለም። ዕብ ፱፣፲፪

🛑ራሱንም ለዅሉ #ቤዛ ሰጠ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ። ፩ኛ ወደ ጢሞቴዎስ ፪፣፮

🛑እርሱ ከጨለማ ሥልጣንአዳነን #ቤዛነቱንም እርሱንም የኀጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን። ፩ኛ ቆላስይስ ፩ ፲፫-፲፬

🛑እግዚአብሔር የሰጠን የምንድንበት በእርሱ ተስፋ የምንኖርበት የልጁ #ቤዛ ይሁን አለችው። ጦቢት ፭፣፭

🛑ስለ ሁለት መቶ ሰባ ሶስት #ቤዛ በየራሱ አምስት ሰቅል ውሰድ። ኦሪት ዘ ትልቅ ፫

🛑ሰው ስለነፍሱ #ቤዛ ምን ይሰጣል? ማቴ ፲፮፣፳፮

🛑እንዲሁም የሰው ልጅ ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች #ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም። ማቴ ፳፣፳፰

🛑ሊያገለግልና ነፍሱን ለብዙዎች #ቤዛ ሊሰጥ እንጅ እንዲያገለግሉት አልመጣም። ማር፲

🛑ጎብኝቶ ለህዝቡ #ቤዛ አድርጓልና ሉቃ ፩፣፴፰

🛑ሰውስ ስለነፍሱ #ቤዛ ምን ይሰጣል? ማር፰፣፴፯

🛑የኢሩሳሌምንም #ቤዛ ለሚጠባበቁ ሁሉ ስለእርሱ ይናገር ነበር። ሉቃ ፪፣፴፰

🛑ክፉ ቃል ከአፋችኹ ከቶ አይውጣ።

#ለቤዛም ቀን የታተማችኹበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ። ፩ኛ ኤፌ ፬፣፳፱-፴

🛑በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በኃይልና በብዙ ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል። ይህም ሊሆን ሲጀምር #ቤዛችሁ ቀርቦአልና አሻቅባችሁ ራሳችሁን አንሡ። ሉቃ ፳፩፣፳፯-፳፰

🛑ነገር ግን የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደተጻፈው ይኾን ዘንድ ከእግዚአብሔር ዘንድጥበብና ጽድቅ፣ ቅድስናም፣ #ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የኾናችኹ ከእርሱ ነው። ፩ኛ ቆሮ፩፣፴-፴፩

🛑በደሙ የተገኘ #ቤዛችንን አገኘን። ኤፌሶን ሰዎች ፩

🛑የመንፈስ በኵራት ያለን ራሳችን ደግሞ የሰውነታችን #ቤዛ የኾነውን ልጅነት እየተጠባበቅን…ሮሜ ፰

🛑ሙሴንበመልአኩ እጅ እግዚአብሔር ሹምና #ቤዛ አድርጎ ላከው። የሐዋርያት ስራ ፯

🛑በኢየሱስ ክርስቶስም በኾነው #ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ። ሮሜ ፫

May be a graphic of text