
የፊደላችን እያንዳንዱ በግዕዝ ትርጉም አላቸው!
ሀ – ማለት ሀልዎቱ ለአብ እምቅድመ ዓለም ማለት ነው፡፡
ኀ ማለት ኀብአ ርእሶ ማለት ነው፡፡
ሁ ማለት ኪያሁ ተወከሉ ማለት ነው፡፡
ሑ ማለት ሰብሑ ለሥመ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ኁ ማለት እኁዝ አቅርንቲሁ ማለት ነው፡፡
ሂ ማለት አስተይዎ ብሂዐ ማለት ነው፡፡
ሒ ማለት መንጽሒ ማለት ነው፡፡
ኂ ማለት ዘልማዱ ኂሩት ማለት ነው፡፡
ሃ ማለት ሃሌ ሉያ ማለት ነው፡፡
ሓ ማለት መፍቀሬ ንስሓ ማለት ነው፡፡
ኃ ማለት ኃያል በኃይሉ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ሄ ማለት በኵለሄ ሀሎ ማለት ነው፡፡
ሔ ማለት ሔት ሕያው እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ኄ ማለት ኄር እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ህ ማለት ህልው እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ሕ ማለት ሕያው እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ኅ ማለት ኅብስት ለርኁባን ማለት ነው፡፡
ሆ ማለት ኦሆ ይቤ ወመጽአ ማለት ነው፡፡
ሖ ማለት ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ኆ ማለት ኆኅተ ገነት ወልድ ማለት ነው፡፡
ኈ ማለት ኈለቈ አዕፅምትየ ማለት ነው፡፡
ኋ ማለት ሰንኋቲ ሥጋ ሰብእ ማለት ነው፡፡
ኌ ማለት ይኌልቍ አሥዕርተ ማለት ነው፡፡
ኊ ማለት በኊበኊ ሥጋ አዳም ማለት ነው፡፡
ኍ ማለት ዑጽፍት ወኍብርት ማለት ነው፡፡
ለ ማለት ለብሰ ሥጋ ዚአነ ማለት ነው፡፡
ሉ ማለት ሣህሉ ለእግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ሊ ማለት ከሃሊ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ላ ማለት ላሜድ ልዑል እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ሌ ማለት መቅለሌ ዕጹብ ማለት ነው፡፡
ል ማለት መስቀል ዘወልደ አብ ማለት ነው፡፡
ሎ ማለት ዘሀሎ እምቅድም ማለት ነው፡፡
መ ማለት መንክር ግብሩ ለእግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ሙ ማለት ሙፃአ ሕግ ማለት ነው፡፡
ሚ ማለት ዓለመ ኀታሚ ማለት ነው፡፡
ማ ማለት ፌማ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው፡፡
ሜ ማለት ሜም ምዑዝ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ም ማለት አምላከ ሰላም ማለት ነው፡፡
ሞ ማለት ሞተ በሥጋ ማለት ነው፡፡
ሰ ማለት ሰብአ ኮነ ከማነ ማለት ነው፡፡
ሠ ማለት ሠረቀ በሥጋ እምድንግል ማለት ነው፡፡
ሱ ማለት ፋሲልያሱ ማለት ነው፡፡
ሡ ማለት መንበረ ንግሡ ማለት ነው፡፡
ሲ ማለት ዘይሴሲ ለኲሉ ዘሥጋ ማለት ነው፡፡
ሢ ማለት ሢመተ መላእክት ማለት ነው፡፡
ሳ ማለት ሳምኬት ስቡሕ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ሣ ማለት ሣህል ወርትዕ ማለት ነው፡፡
ሴ ማለት ለባሴ ሥጋ ማለት ነው፡፡
ሤ ማለት ሤሞሙ ለካህናት ማለት ነው፡፡
ስ ማለት ልብስ ለዕሩቃን ማለት ነው፡፡
ሥ ማለት ንጉሥ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ሶ ማለት መርሶ ለአሕማር ማለት ነው፡፡
ሦ ማለት አንገሦ ለአዳም ማለት ነው፡፡
ረ ማለት ረግዓ ሰማይ ወምድር በጥበቡ ማለት ነው፡፡
ሩ ማለት በኵሩ ለአብ ማለት ነው፡፡
ሪ ማለት ዘይሰሪ አበሳ ማለት ነው፡፡
ራ ማለት ጌራ መድኃኒት ማለት ነው፡፡
ሬ ማለት ሬስ ርኡስ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ር ማለት ርግብ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው፡፡
ሮ ማለት ፈጠሮ ለዓለም ማለት ነው፡፡
ቀ ማለት ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ ቃል ወውእቱ ቃል ኀበ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ቁ ማለት ጽድቁ ለኃጥእ ማለት ነው፡፡
ቂ ማለት ፈራቂሁ ለዓለም ማለት ነው፡፡
ቃ ማለት ቃልየ አጽምዕ ማለት ነው፡፡
ቄ ማለት ሰዋቄ ኃጥአን ማለት ነው፡፡
ቅ ማለት ጻድቅ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ቆ ማለት ቆፍ ቅሩብ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ቈ ማለት ተኈለቈ ምስለ ጊጉያን ማለት ነው፡፡
ቊ ማለት ቊርባነ ወንጌል ማለት ነው፡፡
ቍ ማለት ቍየጺሁ አዕማደ ባላቅ ማለት ነው፡፡
ቌ ማለት ቀነተ ሐቌሁ ለኀጺበ እግረ አርዳኢሁ ማለት ነው፡፡
በ ማለት በትሕትናሁ ወረደ ለቤዛ ኵሉ ዓለም ማለት ነው፡፡
ቡ ማለት ጥበቡ ለአብ ማለት ነው፡፡
ቢ ማለት ረቢ ነአምን ብከ ማለት ነው፡፡
ባ ማለት ባዕድ እምአምአማልክተ ሐሰት ማለት ነው፡፡
ቤ ማለት ቤት ባዕል እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ብ ማለት ብርሃነ ቅዱሳን ፍጹማን ማለት ነው፡፡
ቦ ማለት አልቦ ባዕድ አምላክ ዘእንበሌሁ ማለት ነው፡፡
ተ ማለት ተሰብአ ወተሠገወ እማርያም እምቅድስት ድንግል ማለት ነው፡፡
ቱ ማለት መዝራዕቱ ለአብ ማለት ነው፡፡
ቲ ማለት ተአኳቲ ለእግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ታ ማለት ታው ትጉህ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ቴ ማለት ከሣቴ ብርሃን ማለት ነው፡፡
ት ማለት ትፍሥሕት ወሐሤት ማለት ነው፡፡
ቶ ማለት ነአምን ልደቶ ለክርስቶስ ማለት ነው፡፡
ነ ማለት ነሥአ ደዌነ ወጾረ ሕማመነ ማለት ነው፡፡
ኑ ማለት ዛኅኑ ለባሕር ማለት ነው፡፡
ኒ ማለት ኰናኒ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ና ማለት መና እስራኤል ማለት ነው፡፡
ኔ ማለት ወጣኔ ኵሉ ማለት ነው፡፡
ን ማለት መኰንን እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ኖ ማለት ኖላዊ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
አ ማለት አአኵቶ ወእሴብሖ ለእግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ዐ ማለት ዐቢይ እግዚአብሔር ወብዙኅ አኮቴቱ ማለት ነው፡፡
ኡ ማለት ሙጻኡ ለቃል ማለት ነው፡፡
ዑ ማለት ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ኢ ማለት ለሊሁ ተንሣኢ ወለሊሁ አንሣኢ ማለት ነው፡፡
ዒ ማለት ለሊሁ ሠዋዒ ወለሊሁ ተሠዋዒ ማለት ነው፡፡
ኣ ማለት ኣሌፍ ፈጣሬ ኵሉ ዓለም ቀዳማይ ወደኃራዊ ማለት ነው፡፡
ዓ ማለት ዓይነ ኵሉ ነፍስ ይሴፎ ኪያከ ማለት ነው፡፡
ኤ ማለት አምጻኤ ዓለማት ማለት ነው፡፡
ዔ ማለት ዔ ዐቢይ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
እ ማለት እግዚአብሔር እግዚእ ማለት ነው፡፡
ዕ ማለት ብፁዕ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ኦ ማለት እግዚኦ ማለት ነው፡፡
ዖ ማለት ሞዖ ለሞት ወተንሥአ ማለት ነው፡፡
ከ ማለት ከሃሊ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ኩ ማለት ዐርኩ ለመርዓዊ ማለት ነው፡፡
ኪ ማለት ኪያሁ ንሰብክ ማለት ነው፡፡
ካ ማለት ካፍ ከሃሊ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ኬ ማለት ሰባኬ ወንጌል ነዋ በማእከለ አኃው ማለት ነው፡፡
ክ ማለት ክብሮሙ ለመላእክት ማለት ነው፡፡
ኮ ማለት ዘረዳእኮ ለአብርሃም ማለት ነው፡፡
ኳ ማለት ኳሄላ አይሁድ ወልድ ማለት ነው፡፡
ኰ ማለት ኰናኔ ዓለም ማለት ነው፡፡
ኵ ማለት ኵርጓኔ ቅዱሳን ማለት ነው፡፡
ኲ ማለት ኲናተ ጌዴዎን ዘቈልቈለ ላዕለ ስሳ ምዕት ሐራ በምዕር ማለት ነው፡፡
ኴ ማለት ወይኴንን እምባሕር እስከ ባሕር ማለት ነው፡፡
ወ ማለት ወረደ እምሰማያት ማለት ነው፡፡
ዉ ማለት ጼዉ ለምድር ማለት ነው፡፡
ዊ ማለት ናዝራዊ ሐዊ ማለት ነው፡፡
ዋ ማለት ዋው ዋሕድ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ዌ ማለት ዜናዌ ትፍሥሕት ማለት ነው፡፡
ው ማለት ሥግው ቃል ማለት ነው፡፡
ዎ ማለት ቤዘዎ ለዓለም ማለት ነው፡፡
ዘ ማለት ዘኲሎ ይእኅዝ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ዙ ማለት ምርጒዙ ለሐንካሳ ማለት ነው፡፡
ዚ ማለት ናዛዚ ማለት ነው፡፡
ዛ ማለት ዛይ ዝኲር እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ዜ ማለት አኃዜ ዓለም በእራኁ ማለት ነው፡፡
ዝ ማለት ሐዋዝ ሕገ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ዞ ማለት አግአዞ ለአዳም ማለት ነው፡፡
የ ማለት የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኀይለ ማለት ነው፡፡
ዩ ማለት ዕበዩ ለእግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ዪ ማለት መስተሥርዪ ማለት ነው፡፡
ያ ማለት አንተ ኬንያሁ ማለት ነው፡፡
ዬ ማለት ዐሣዬ ሕይወት ማለት ነው፡፡
ይ ማለት ሲሳይ ለርኁባን ማለት ነው፡፡
ዮ ማለት ዮድ የማነ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ደ ማለት ደመረ መለኮቶ ምስለ ሥጋነ ወሥጋነ ምስለ መለኮቱ ማለት ነው፡፡
ዱ ማለት ፈዋሴ ዱያን ማለት ነው፡፡
ዲ ማለት ቃለ ዐዋዲ ማለት ነው፡፡
ዳ ማለት ዳሌጥ ድልው እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ዴ ማለት ዐማዴ ሰማይ ወምድር ማለት ነው፡፡
ድ ማለት ወልድ ዋሕድ ማለት ነው፡፡
ዶ ማለት ፈነወ ዋሕዶ ወተሰብአ ማለት ነው፡፡
ገ ማለት ገባሬ
ሰማያት ወምድር ማለት ነው፡፡
ጉ ማለት ለአስካለ ሕይወት ሐረጉ ማለት ነው፡፡
ጊ ማለት ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ጋ ማለት ጋሜል ግሩም እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ጌ ማለት ጽጌ ቅዱሳን ማለት ነው፡፡
ግ ማለት ሐጋጌ ሕግ ማለት ነው፡፡
ጐ ማለት ጐሥዐ ልብየ ቃለ ሠናየ ማለት ነው፡፡
ጕ ማለት ስንጓጕ እምኃጢአት ማለት ነው፡፡
ጒ ማለት ጒንደ ሐረገወይን ወልድ ማለት ነው፡፡
ጓ ማለት ዕጓለ እመሕያው ማለት ነው፡፡
ጔ ማለት ዝንጓጔ መስቀል ማለት ነው፡፡
ጕ ማለት ስንጓጕ እምኃጢአት ማለት ነው፡፡
ጠ ማለት ጠቢብ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ጡ ማለት ውስጡ ለሰብእ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ጢ ማለት መያጢሆሙ ለኃጥአን ማለት ነው፡፡
ጣ ማለት የውጣ እንተ አሐቲ ሕርመታ ማለትነው፡፡
ጤ ማለት ጤት ጠቢብ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ጥ ማለት ስሉጥ ወርኡስ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ጦ ማለት ሦጦ ለመንፈስ ቅዱስ ላዕሌነ ማለት ነው፡፡
ጰ ማለት ጰራቅሊጦስ መንፈሰ ጥድቅ ማለት ነው፡፡
ጱ ማለት ኮጱ መዓዛ ሰብእ ማለት ነው፡፡
ጲ ማለት ሠራጲሁ ለዓለም ማለት ነው፡፡
ጳ ማለት ጳጳስ ወንጌል ማለት ነው፡፡
ጴ ማለት አክራጴ ኃጢአት ማለት ነው፡፡
ጵ ማለት ጵርስፎራ ማለት ነው፡፡
ጶ ማለት ጶሊስ ማለት ነው፡፡
ጸ ማለት ጸጋ ወጽድቅ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ፀ ማለት ፀሐየ ጽድቅ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ጹ ማለት ገጹ ለአብ ማለት ነው፡፡
ፁ ማለት ዮም ሠረፁ ጽጌ በረከት ማለት ነው፡፡
ጺ ማለት ሐዋጺ ነፍሰ ትሑታን ማለት ነው፡፡
ፂ ማለት መላፂ ዘክልኤ አፉሁ ማለት ነው፡፡
ጻ ማለት ጻዴ ጻድቅ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ፃ ማለት ፋፃ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው፡፡
ጼ ማለት አዕቃጼ ሰኮና ማለት ነው፡፡
ፄ ማለት ሕፄሁ ለዳዊት ማለት ነው፡፡
ጽ ማለት ጽንሁ ተስፋሁ ማለት ነው፡፡
ፅ ማለት ዕፅ አብርሃም ዘሰፀረ ለምስዋዕ ማለት ነው፡፡
ጾ ማለት ጾም ትፌውስ ቊስለ ነፍስ ማለትነው፡፡
ፆ ማለት ማዕፆ አፉሆሙ ለጻድቃን ማለት ነው፡፡
ፈ ማለት ፈጠረ ዓለመ በጥበቡ ማለት ነው፡፡
ፉ ማለት ምዕራፉ ለዓለም ማለት ነው፡፡
ፊ ማለት ፊደለ ወንጌል ዘአባ ኀነፊ ማለት ነው፡፡
ፋ ማለት አልፋ ወኦ ማለት ነው፡፡
ፌ ማለት ኀዳፌ ነፍሳት ማለት ነው፡፡
ፍ ማለት ፍኖት ለኀበ አቡሁ ማለት ነው፡፡
ፎ ማለት ፎራ ኅብስተ ቍርባን ማለት ነው፡፡
ፐ ማለት ፓፓኤል ስሙ ለእግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ፑ ማለት ኖፑ አስካለ ወንጌል ማለት ነው፡፡
ፒ ማለት ፒላሳሁ ማለት ነው፡፡
ፓ ማለት ፓንዋማንጦን ማለት ነው፡፡
ፔ ማለት ፔ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ፕ ማለት ሮፕ ጽኑዕ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡
ፖ ማለት በቀዳሚ ገብረ እግዚአብሔር ሰማየ ወምድረ ወበደኃሪ የኀልፎ ለዓለም ማለት ነው፡፡
የፊደላትን ትርጉም በአግባቡ ከተረዳን በዝተዋል ይቀነሱ የሚሉትን ሰዎች ማስረዳት ከመቻላችንም በላይ ፊደላትን ያለቦታቸው ከመጠቀም እንቆጠባለን፡፡
