
24 ጥቅምት 2025
ጣና ፎረም ለሰላም እና የደኅንነት ችግሮች አፍሪካ መር መፍትሔ ለመስጠት ጥሪ ያቀረበውን የትሪፖሊ ቃል ኪዳንን ተከትሎ የተጀመረ ጉባኤ ነው።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስር በሚገኘው የሰላም እና ደኅንነት ጥናት ተቋም እንዲሁም በፍሪካ ታዋቂ መሪዎች አነሳሽነት የተመሠረተው ፎረሙ፤ ዓላማው በአህጉሪቱ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ መሪዎች፣ ውሳኔ ሰጪዎች እና ባለሙያዎች እንዲመካከሩ፣ ሀሳብ እንዲለዋወጡ ልዩ መድረክ መፍጠር ነው።
በ2004 ዓ.ም. (እአአ በ2012) በባሕር ዳር ከተማ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንትኦሊሴጉን ኦባሳንጆ የጣና ፎረም ጉባኤ የመጀመሪያ ሊቀ መንበርነት ሆነው ነበር ጉባኤው የተጀመረው።
ከሁለት ዓመት መቋረጥ በኋላ 11ኛው የፎረሙ ጉባኤ አርብ ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም. ከዓመታት በኋላ በባሕር ዳር ከተማ ተጀምሯል።
ከፍተኛ የደኅንነት ጉባኤ የሆነው ጣና ፎረም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሰላም እና ደኅንነት ጥናት ተቋም የሚዘጋጅ ነው።
