
Yared Hailemariam ·Follow
መልዕክተ ቅዳሜ፤
መንግስታዊ መክሸፍ (Governance failure)
++++++
በቴሌግራም ለመከታተል፤ https://t.me/yaredH_2024
በዛሬው መልዕክተ ቅዳሜ አንድ ሀገር በከሸፈ ወይም አገር የማስተዳደር ብቃት ባጣ ጏይል እጅ ሥር ስትወድም ምን ልትመስል እንደምትሽል የብልጽግናን አቋምና የዛሬዋን ኢትዮጵያ ሁናታ በመገምገም ላይ የሚያተኩር ነው። አንባቢዎቼን አስቀድሜ ለማሳሰብ የምወደው ትኩረቴ በ failed state ላይ ሳይሆን failed governance ላይ መሆኑን ነው። ሁለቱ አንዱ ሌላውን ተከትሎ የሚመጣ ነገር ቢሆንም ፍጹም የተለያዩ ነገሮች ናቸው።
አንድ አገር እያስተዳደረ ያለ የፖለቲካ ድርጅት ወይም ቡድን ከሸፈ፣ ውዳቂ ሆነ፣ አገር ለማስተዳደር የሚያስችል አቅምም ሆነ ብቃት የለውም፣ ደካማና ልፍስፍስ ነው የሚባለው መቼ እን ምን ሁኔታዎች ሲሟሉ ነው የሚለውን መጀመሪያ በግርድፉ እንመልከት። አንድ የመንግስትን መንበር ላይ የተቆናጠጠ ጏይል የሕግ የበላይነትን አረጋግቶ፣ ሰላምና ጸጥታን አስጠብቆ፣ የመንግስታዊ መዋቅሮችን በአግባቡ አደራጅቶ ሥርዓት በያዘ መንገድ ተቋማቱ የተፈጠሩለትን እና በሕግ የተጣለባቸውነ ሃላፉነቶች በአግባቡ ተናበው በቅንጅትም ሆነ በተናጠል መምራት ሲችል፣ የአገሪቱን ሉዐላዊነት እና የዜጎቹን ደህንነት መጠበቅና ማስጠበቅ ሲችል እና ልማት ላይ ያተኮረ የኢኮኖሚ መሠረት መገንባትና በየጊዜው እድገትና መሻሻል ማስመዝገብ ሲችል ነው የመንግስትነት ሥራውን በብቃት እየተወጣ ወይም ለመወጣት እየጣረ ነው የሚባለው።
ከላይ ያሉትን ጏላፊነቶች መወጣተት የተሳነው፣ ያልቻለና አቅሙ ያልፈቀደለት ቡድን ውዳቂ ወይም አቅመ ቢስ ይባላል። ሦስት አይነት የመንግስታዊ ሥርዓት መውደቅ መገለጫዎች አሉ። እነሱም፤
1ኛ/ Corporate failure የመጀመሪያው ሲሆን ይህም ቁልፍ የሆኑ የመንግስት ተቋማት አመራሮች ላይ በሚፈጠር ድክመት የተነሳ በተተለይም ወደ ውንብድና ያደሉ የተቀናጁ ዝርፊያዎችን ተከትሎ የሚከሰት የኢኮኖሚ መላሸቅ፣ የሥራ ተነሳሽነት መጥፋት እና የሲስተሞች መዛባት የሚያስከትለው ነው።
2ኛ/ State & Political Failure: ይሄ የአንድ ወይም የተወሰኑ ተቋማት መክሸፍ ሳይሆን ራሱ አገረ መንግስቱ እና የፖለቲካ መዋቅሩ መሠረታዊ የሆኑ የአገርና የዜጎችን ደህንነት መጠበቅና ማስጠበቅ ሲሳነው ነው። ለዚህ ብዙ ጊዜ ሶማሌ ነበረች እንደ ሀገር የምትጠቀሰው።ይህ አይነቱ ልሽቀት የአገዛዝ ሥርዓቱ ስር የሰደደ የመምራት አቅም ማጣትን ተከትሎ የሚመጣ በመሆኑ አገሪቱ በግጭቶች፣ በጦርነቶችና በከፍተኛ የሆነ ተቃርኖና ጥላቻ አዘል ልዩነቶችን የምታስተናግድ በመሆኑ መንግስት ቦታ ላይ የተቀመጠው አካል በብሔራዊ ደረጃ በቂ በጀት መመደብን ጨምሮ ተቋማተቶቹ በሙሉ አቅማቸው እንዲሰሩ ማድረግ አይችልም።
3ኛ/ Global Governance Failure: ይሄ ደግሞ በአለም አቀፍ፣ በአህጉርና ቀጠናዊ ትብብሮች፣ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶች፣ የኢኮኖሚ ትስስሮችና ሌሎች የፖለቲካ ጉዳዬች ላይ እጅግ ደካማ፣ በሌሎች ተጽዕኖ ስር ሙሉ በሙሉ የወደቀ፣ ተጽዕኖ መፍጠር የማይችል፣ የድንበርም ሆነ ሌሎች የሉአላዊነት መገለጫ የሆኑ ጉዳዮችን በበቂ ሁኔታ ማስጠበቅ የማይችል ጏይል ሲሆንና በዚህ ድክመቱም ምክንያት አገሪቱን ወደ ድንበር ተሻጋሪ ግጭቶች፣ የሌሎች አገሮች ጉዳይ ፈጻሚ ወደማረግ ወይም ሌሎች አገሮች አገሪቱንና ዜጎቿን ሲንቁና ያለምንም ከልካይ ያሻቸውን ሲያደርጉ ማስቆም የማይችል ሲሆን ነው።
ይህን መነሻ አድርገን በመደመር እሳቤ በሚመራው ብልጽግና እጅ የወደቀችውን ኢትዮጵያ እና መሪዎቹን እንመልከት። እንደ እኔ ግምገማ ብልጽግና በሦስቱም መስፈርት failed governance መሆኑን በተጨባጭ ካሳየ ውሎ አድሯል። የብልጽግና ክሽፈት ግን ከሚገመተውም በላይ እጅግ እጅግ የወረደ በመሆኑ አገሪቱንም ጭምር ይዞ ሊጠፋ እየተውረገረገ ያለበት ሁኔታ ውስጥ ነው የሚገኘው።
አንዳንድ failed government ቶሎ የእርምት እርምጃዎችን በመውሰድ፣ ፖሊሲዎችን በመቀየር፣ ተቋማቶችን በማጠናከር ጨርሶ ከመንኮታኮት እራሳቸውንም አገራቸውንም ይታደጋሉ። ብልጽግና ግን እነዛንም እድሎች ካጣቸው ውሎ አድሯል። አሁን የቀረው አማራጭ ብልጽግና ብቻውን ይክሰም ወይስ አገሪቷንም ይዞ አብሮ ይንኮታኮት የሚለው ነው። እሱን ደግሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው የሚወስነው። ከፈቀደላቸው ግን እንጦሮጦስ ይዘው ከመውረድ የሚመለሱ አይደሉም።
ኢትዮጵያ ዛሬ በኢኮኖሚው፣ በፖለተቲካው፣ በጸጥታና ደህንነት፣ በሉዐላዊነት ዙሪያ እየከፈለች ያለቻቸው ከፍተኛ ዋጋዎች ከብልጽግና እጅግ ደካማ የሀሆነ የማስተዳደር ብቃት መታጣት የመነጩ ናቸው። አብይ እንደግለሰብ እና በሱ የመደመር ፍልስፍና የሚመራው ድርጅት፤ ብልጽግና የአቅም ችግር ብቻ ሳይሆን ቅንነት የጎደለው፣ ድንቁርናም የተጫነው፣ አገር የማስተዳደር እውቀትና ብልሃቱ የጠፋው፣ በሙስና አንገቱ ድረስ የተዘፈቀ፣ በጥላቻም የተሞላ እና ጭካኔን መገለጫው ያደረገ ጏይል መሆኑን መዘርዘር ለቀባሪው እንደማርዳት ይቆጠራል። ኢትዮጵያን ለማዳን ብልጽግናን ማስወገድ ብቻ መፍትሔ ሆኖ ይታየኛል። እሱም ግን ካልዘገየ ነው።
መልካም ሰንበት!!

