April 8, 2026


ቦርከና ዜና
የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ ( ኢሕአፓ ) በአገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታና ሊካሄድ በታቀደው ምርጫ ዙሪያ ያለውን ጠንካራ ተቃውሞ ለመግለጽ ለሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ አቀረበ። “ምርጫው አምባገነንነትን የሚያጠናክር የመሸወጃ ትርዒት ነው” ሲል የገለጸው ፓርቲው፣ ሰልፉን የጠራባቸውን ዋና ዋና ምክንያቶች በመግለጫው ይፋ አድርጓል፦
ከእነዚህም ውስጥ
- ነፃ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል “አስቻይ ሁኔታ” አለመኖሩ።
- በትግራይ፣ በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ያለው የጦርነት ወላፈን ሳይቆም እንዲሁም ንጹሐን በድሮንና በከባድ መሣሪያ ጥቃት እየተገደሉ ምርጫ ማካሄድ አደገኛ መሆኑ።
- ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በታሰሩበት እና ሚዲያዎች በጫና ሥር ባሉበት ሁኔታ ምርጫው ተቀባይነት የለውም ማለቱ።
- በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በረሃብና በድህነት እየማቀቁ መሆኑ።
የፓርቲው ጥሪና ጥያቄዎች፡
- የንጹሐን ጭፍጨፋና አፈና በአስቸኳይ እንዲቆም።
- የፖለቲካ እስረኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ።
- የኑሮ ውድነትን የሚገቱ እርምጃዎች እንዲወሰዱ።
ሰልፉ ከአንድ ወር በኋላ ዓርብ ሚያዝያ 30 ቀን በሚከተሉት ከተሞች ይካሄዳል ተብሏል፦
አዲስ አበባ
መቀሌ
ባሕር ዳር
ጎንደር
ሐዋሳ
አሶሳ
አዳማ
አምቦ
ድሬዳዋ
ሐረር
ኢሕአፓ “ለሕዝብ ስቃይ መቀጠል ምክንያት የሚሆንን ሂደት እንቃወማለን” ሲል መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለጥሪው ምላሽ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
– Advertisement –

የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ ፡ t.me/borkena
ፌስቡክ ገጻችንን ላይክ ያድርጉ ፡ Borkena
