April 24, 2026

በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ብልጽግና ፓርቲን በመወከል በአዲስ አበባ ከተማ ለፓርላማ አባልነት ዕጩ ሆነው ቀርበው የነበሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተተኩ። ዶ/ር ሳሙኤል ከምርጫው ራሳቸውን ያገለሉት “በግል ምክንያት” እንደሆነ ለ“ምርጫ 2018 – ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

ዶ/ር ሳሙኤል ገዢው ፓርቲ በአዲስ አበባ ከተማ ለፓርላማ እንዲወዳደሩ ካቀረባቸው 20 ዕጩዎች መካከል አንዱ ነበሩ። ዕጩው በስድስተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲን በመወከል ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ተመርጠው እንደነበር ይታወሳል።

ብልጽግና ፓርቲ ባለፈው መጋቢት ወር መጀመሪያ ይፋ ባደረገው የዕጩዎች ዝርዝር፤ ዶ/ር ሳሙኤል ፓርቲውን በመወከል በአራዳ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ምርጫ ክልል 2 እና 14 ለፓርላማ እንደሚወዳደሩ አስታውቆ ነበር። ዶ/ር ሳሙኤል ገዢው ፓርቲ ባዘጋጃቸው የዕጩዎች ማስተዋወቂያ ይፋዊ መድረኮች ላይ በመገኘት ተወዳዳሪነታቸውን አረጋግጠዋል።

ሆኖም የእርሳቸው ዕጩነት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኃላፊነታቸው ጋር የሚቃረን መሆኑን በህግ በማስደገፍ የገለጹ ወገኖች ተወዳዳሪነታቸውን ጥያቄ ውስጥ ከተውታል። እነዚህ ወገኖች የሚጠቅሱት ድንጋጌ፤ የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎችን ለመደንገግ በ2016 ዓ.ም በወጣ አዋጅ ላይ የተካተተ ነው።

ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ፦ https://ethioelections.com/2026/04/17528/