“አንድ እስረኛ ተመርምሮ ሲመለስ መጀመሪያ የሚቀርብለት ጥያቄ ‘ተሰቅለህ ነበር ወይም አልተሰቀልክም?’ የሚል ነው የሚሉት ከእስር የተለቀቁት አቶ ሐብታሙ አያሌው ለማመን የሚከብድ ከባድ መከራዎች በእስር ቤት ውስጥ እንደሚፈፀም ይናገራሉ። አቶ ሃብታሙ አያሌው በዚህ ፕሮግራም ላይ ስለ ምርመራ ዓይነቶች በዘረዘሩበት ወቅት የሰጡት ማብራሪያ እጅግ ዘግናኝ በመሆኑ ሕጻናት ልጆች እንዳያደምጡት የወላጆችን ትብብር እንጠይቃለን። የቃለምልልሱ ሁለተኛ ክፍል ቅዳሜ ምሽት ይቀርባል።
ዋሽንግተን ዲሲ — የቀድሞው የተቃዋሚው አንድነት ፓርቲ ቃል አቀባይ በሽብር ወንጀል ተከሰው እሥር ቤት በቆዩባቸው ሁለት ዓመታት በምርመራ ሳቢያ ደረሰብኝ ያሉት ከባድ ስቃይ አሁን ለሚገኙበት የጤና ቀውስ እንደዳረጋቸው ይናገራሉ።ወህኒ ቤቶች ውስጥ የሚፈጸሙ ጭካኔ የተሞላባቸው ልዩ ልዩ የምርመራ ዓይነቶች በአብዛኞቹ እሥረኞች ላይ ሕልፈትን ጨምሮ ለተመሳሳይ የጤና ችግሮች እንደሚዳርጉም አቶ ሃብታሙ ያስረዳሉ።
አቶ ሃብታሙ አያሌው በዚህ ፕሮግራም ላይ ስለ ምርመራ ዓይነቶች በዘረዘሩበት ወቅት የሰጡት ማብራሪያ እጅግ ዘግናኝ በመሆኑ ሕጻናት ልጆች እንዳያደምጡት የወላጆችን ትብብር እንጠይቃለን። አቶ ሃብታሙ አያሌውን ያነጋገራቸው የፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ሰሎሞን ክፍሌ ነው።
አቶ ሃብታሙ ደረሱብኝ ያሏቸውን በደሎች በሚዘረዝሩበት ይጀምራሉ። – VOA Amharic
አድማጮች የዚህ ቃለምልልስ ሁለተኛ ክፍል ቅዳሜ ምሽት ይቀርባል።