ለመድመጥ ይህን ይጫኑ⇓
አዎንታዊ ምላሽ ካልተገኘ ውይይቱን ሊያቋርጡ እንደሚችሉ መድረክ አስጠነቀቀ
22 ፓርቲዎች በሚሳተፉበት ሸንጎ ላይ መደራደር እንደማይቻልና የመድረክ ፍላጎት ከገዢው ፓርቲ ኢሐዴግ እና ከመንግሥት ጋር ብቻውን መደራደር እንደሆነ የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጼጥሮስ ተናግረዋል።
በድርድሩ አካሄድ ላይ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ ካላገኘ ውይይቱን ሊያቋርጡ እንደሚችሉ የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ተናገሩ። መድረክ መሪ ተዳዳሪ ሆኖ እንዲቀርብ አለበለዚያም ጎን ለጎንና ብቻውን ከገዢው ፓርቲ ጋር እንዲደራደር ጥያቄ ሲያቀርብ ቆይቷል።22 ፓርቲዎች በሚሳተፉበት ሸንጎ ላይ መደራደር አይቻልም ብለዋል ፕሮፌሰር በየነ።