ያሬድ ኃይለማርያም ለ7 ዓመታት ያህል ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ካውንስል ጋር አብሮ የሠራና የኖቬምበር 1 እማ 2ቱን ጭፍጨፋ ተከትሎ ከሃገር ብዙ ምስጢሮችን ይዞ በመውጣት ለአውሮፓ ሕብረት ያቀረበ ነው።

ዶ/ር ቴውድሮስ የወያኔ የአገዛዝ ስርዓት በኢትዮጵያ ውስጥ ላለቱት አሥርት አመታት ለፈጸማቸው የሰብአዊ መብት ጥሰቶችና የግፍ ተግባራት ቀጥተኛ ተጠያቂ ከሆኑት የስርዓቱ ቁንጮዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ዳኛ የለም እንጂ ዳኛማ ቢኖር … ይህ ሰው ሕግ ፊት ቀርቦ በአገሪቱ ማጎሪያ ቤቶች ሕክምና እየተነፈጉ ላለቁትና ዛሬም እየማቀቁ ላሉት ሰዎች፤ እንዲሁም ኦጋዴንን ጨምሮ በበርካታ የአገሪቱ ክፍሎች በሕክምና እጦት ለሚሰቃዩት ሰዎች ሁሉ ተጠያቂ በተደረገ ነበር፡፡

ቴውድሮስና ግብራበሮቹ የወያኔ ባለስልጣናት በቪላ ቤቶች፣ በሚሊዮኖች በተገዙ ውድ መኪኖች ሲንደላቀቁ እና ጥቂቶች የአገሪቱን ሃብት ተቀራምተው በሙስና ሲጨማለቁ የአገሬ ደሃ ሕዝብ አንዲት መርፌና እፍኝ ኪኒን መግዣ ጠሮበት፣ የወባ አጎበር መግዛት አቅቶት፣ ለልጆቹ የሚላስ የሚቀመስ ማቅረብ አቅቶት ከፊቱ በጠኔ ሲደፉ ማየት ያሳዝናል፡፡

የፌደራል መንግስቱ መቀመጫና የዶ/ር ቴውድሮስ መዋያና ማደሪያ በሆነችው አዲስ አበባ በቅርቡ የቆሻሻ ክምር ተንዶ በመቶዎች የሚቆጠሩ ወንድም እህቶቻችንን ያጣንበት አሳዛኝ ክስተት የቅርብ ጊዜ ሃዘናችን ነው፡፡ እነ ቴውድሮስ አደሃኖም በአስርት አመታት ጉዞዋቸው ያቆዩልን ኢትዮጵያ ምን እንደምትመስል በትንሹ ለማየት ይቺን የጺዮን ግርማን (Tsion Girma Tadesse) ሪፖርት አድምጧት፡፡

በየመንደሩ ከሄድን ደሞ ከዚህ በብዙ እጥፍ የሚዘገንኑና እንደ ሃገር የሁላችንንም አንገት የሚያስደፉ በርካታ ነገሮችን መታዘን እንችላለን፡፡ እንዲህ አይነቱ አገርንና ሕዝብን አዋራጅ የሆነ ተግባር ሊፈጸም የሚችለው እንደነ ቴውድሮስ አድሃኖም ያሉ ዳተኛና ለሰውልጅ ክብር ግድ የማይሰጣቸው እኩይ ፖለቲከኞች የሥልጣኑን መዘውር ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠሩበት ሃገር ብቻ ነው፡፡ እንደ ቴውድሮስ ያለ ሰው ለፍርድ እንጂ ለአለም አቀፍ የጤና ተቋም መሪነት መመረጥ ቀርቶ የሚታጭ ሰው አይደለም፡