Sunday, 28 May 2017 00:00

ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ስለ ኢቢሲ ምን ይላሉ?

Written by  አለማየሁ አንበሴ

ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ስለ ኢቢሲ ምን ይላሉ?

(ለፖለቲካዊ ችግሮች ፖለቲካዊ ውይይቶች)

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) ተጠሪነቱ ለህዝብ እንደራሴዎች ነው፡፡ ነገር ግን ኮርፖሬሽኑ የህዝብ ሚዲያ አልሆነም የሚሉ ትችቶችና ቅሬታዎች ሲቀርቡበት ቆይቷል፡፡ ኢህአዴግ በ10ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ማጠናቀቂያ ላይ ባወጣው መግለጫ፤ ኢቢሲን ጨምሮ የህዝብ መገናኛ ብዙሃን ለህዝብ ወገንተኛ መሆን እንዳልቻሉ አመልክቶ ነበር፡፡ ከሰሞኑም ኮርፖሬሽኑ ያሉበትን ችግሮች የሚቀርፍ ስር ነቀል ለውጥ እንዲያደርግ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት
ታዟል፡፡ ይህን መነሻ በማድረግ የኮርፖሬሽኑ ዋነኛ ችግሮች ምንድን ናቸው? ለምን የህዝብ አመኔታ ማግኘት ተሳነው? እንዴትስ ተሻሽሎ የህዝብን ቀልብ መግዛት ይችላል? በሚሉ ጥያቄዎች ዙሪያ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ፤ የቀድሞ ማስታወቂያ ሚኒስትር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳን ጨምሮ የተለያዩ ፖለቲከኞችን አነጋግሮ አስተያየታቸውን እንደሚከተለው አጠናቅሯል፡፡