Sunday, 25 June 2017 00:00

  አለማየሁ አንበሴ                                                                                               

በአየር ፀባይ ለውጥ ምክንያት “ኮፊ አረቢካ” በሚል መለያ የሚታወቀውን ተወዳጁ የኢትዮጵያ ቡና ጉዳት እያጋጠመው መሆኑን በመጠቆም የመጥፋት አደጋ እንደተጋረጠበት “ኔቸር ሪሰርች” የተሰኘው ተቋም ባወጣው የጥናት ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡ 
ተቋሙ “ኔቸር ፕላንትስ” በተሰኘው መፅሄቱ ላይ ስለ ታዋቂው የኢትዮጵያ ቡና ያሰፈረውን ሰፊ ዘገባ የእንግሊዙ ዘ ጋርዲያንና ቢቢሲን ጨምሮ በርካታ አለማቀፍ መገናኛ ብዙኃን መነጋገሪያ ጉዳይ አድርገውታል፡፡