June 29, 2017

(ቬሮኒካ መላኩ)

የኦሮሞ ብሔረተኝነት ፖለቲካ ከሌለ የትግራይ ህዝብ አደጋ ላይ ይወድቃል” ገብሩ አስራት

ይሄን ከዚህ በላይ የተፃፈውን የተናገረው የቀድሞው ታጋይ እና የህውሃት ማእከላዊ ኮሚቴ አባል የነበረው ገብሩ አስራት ነው።

በሌላ በኩል የቀድሞው የኦነግ ሊቀመንበር አቶ ሌንጮ ለታ ከሁለት ወር በፊት ከOMN ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ላይ የ OMN ጋዜጠኛ:-

“ኦነግና አንተም በግልህ ረጅም አመታት ታግላችሁ ለኦሮሞ ህዝብ ያመጣችሁት ለውጥ አለ ብላችሁ ታስባላችሁ ወይ?” በማለት ሲጠየቀው አቶ ሌንጮ ቃል በቃል እንደዚህ በማለት መልሶ ነበር።

“ሀሌ ሉያ! የኦሮሞ ህዝብ እኛ ካሰብነው ከገመትነው በላይ ግዛት ያለው ክልል አግኝተናል። ይሄ ትልቅ ስኬት ነው።” በማለት መልሷል።

ዛሬ ይችን እጅግ አጨር ማስታወሻ ለመፃፍ የፈለኩት በተለይ ለአማራ ብሄርተኞች አሁን ያለውን የፖለቲካ ቡድኖች ያለውን የሀይል አሰላለፍ በመገንዘብ ትግላችንን መረር አድርገን እንድንየዘው ለማስታወስ ነው።

ወያኔ የአናሳ ( Minority) ቡድን ነው ።ማንኛውም አናሳ ቡድን ስልጣን ላይ ለመቆየት ዜዴ ያስፈልገዋል። አንዱ ዜዴ ጠመንጃ ነው ጠመንጃው አልሆን ሲል ከብዙሃን ጋር በመጣበቅ ነው።

ህውሃትና የኦሮሞ ብሄርተኞች በፖለቲካ የሀይል አሰላለፍ ብዙ ጊዜ ተመጋጋቢ ናቸው። ህውሃት የኦሮሞ ብሄርተኞችን እንደ ስትራቴጅካል አጋር ሲወስደው በአንፃሩ የኦሮሞ ብሄርተኞች በህውሃት እየተገደሉም ወደ እስር ቤት እየታጎሩም ቢሆን ከህውሃት በሚወረወርላቸው የፖለቲካ ቅንጥብጣቢ በመርካት ህውሃትን እንደ ስልታዊ አጋር ይመለከቱታል።

በዚህ የሃይል አሰላለፍ ውስጥ ሁለቱን ቡድኖች በዚህ ያልተቀሰ ጋብቻ ያቆራኛቸው እንደ አደጋ የሚቆጥሩት የአማራ ህዝብ ነው። እነዚህ ቡድኖች በአይነ ቁራኛ እና በጠላትነት የሚመለከቱት የአማራን የፖለቲካ ሀይል ነው። በህውሃት በኩል የኦሮሞ ብሄርተኞችን የሚጠቀምባቸው እንደ ስልጣን እድሜ ማራዘሚያ የፖለቲካ ኪኒን ሲሆን በኦሮሞ በኩል ከህውሃት የሚወረወረው ቅንጥብጣቢ እስካልቆመ ድረስ ህዝባቸውን የሚመጥን የአገርን መሪነት ቦታ የሚፈልጉ አይመስልም። የኦሮሞ ብሄርተኞች በኢትዮጵያ ለሚደረግ ስር ነቀል ለውጥ አጋር ሊሆኑ አይችሉም። የእነሱ ፍላጎት ስርአቱን በጥገናዊ ለውጥ እንድያደርግ በመርዳት በሂደቱ የፖለቲካ ትርፍራፊ መለቃቀም ነው።

በፖለቲካ አለም አንድ የተለመደ አባባል አለ “በፖለቲካ ውስጥ ዘላቂ ጥቅም እንጅ ዘላቂ ወዳጅም ሆነ ዘላቂ ጠላት የለም ።” ይባላል ። ይሄ አጠቃላይ የሆነ መርህ (General Principle) አሁን ባለው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ለአማራ ህዝብ የሚሰራ አይመስለኝም። ወያኔ ለአማራ ህዝብ ዘላቂ ጠላት እንጅ ጊዚያዊ ወዳጅ መቼም ሊሆን አይችልም።

በዚህ የሃይል አሰላለፍ ለጊዜው አማራው ብቻውን ነው።

አማራው ምን ማድረግ አለበት?

አማራ አሁን ካለው የፖለቲካ ንቃት በተጨማሪ እንደ እሳት የሚንቀለቀልና አስፈላጊ ሲሆን እንደ ቮልካኖ የሚፈነዳ ብሄርተኝነት ማዳበር አለበት።

ጀርመናዊው የማህበረሰብ ፈላስፋ Max Weber “The future will be an Iron Cage” እንዳለው ወደ ፊት ከጠላቶቹ ጋር በዚህ ተመሳሳይ የጉስቁልና እና የጨቋኝ ተጨቋኝ ድራማ የሚያበቃበትና ለውጥ አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት፤ ከለውጡ ቅኝት ጋር ተስማሚ የሚሆን አቋም በመያዝ፤ ለለውጥ ፈላጊው የአማራ ህብረተሰብ ጥያቄ ምላሽ በሚሰጥ አኳኋን ራሳችንን አስተካክለን በመሄድ፤ በፖለቲካዊ ግጭት ምክንያት ሊፈጠር የሚችልን አደጋ በመቀነስ ብሎም በአሸናፊነት ለመወጣት ዝግጁ ሆኖ መጠበቅ ነው።