Skip to content
ሰርፕራይዝ (ካልፎሂያጁ ማስታወሻ የተቀነጨበ)- በውቀቱ ሥዩም
July 20, 2017
(
በ
.
ስ
)
ትናንትና የልደት በአሌን በማስመልከት ከወዳጆቼ አንዱ ወይም አንዲቱ ሰርፕራይዝ ያደርገኛል
/
ታረገኛለች ብየ ብጠብቅ ብጠብቅ ወፍ የለም
::
ግን ተስፋ አልቆረጥኩም
::
ባካባቢየ ወደሚገኝ አንድ ያበሻ ሬስቶራንት ሂጄ ተቀመጥሁ
::
ያዘዝኩት ሰላጣ እስኪመጣ ፌስ ቡኬን ለኮስኩ
::
አንዱ በቀጥታ ካዲሳባ
online
ላይ ጠመደኝ
::
“
ስንት አመትህ ሆነህ ማለት ነው በውቄ
?”
“
ሰላሳ ሰባት
!”
”
ትክክለኛ እድሜህን የማትናገረው ትንሽ በዛ ብለው ግብር እንዳይጥሉብህ ፈርተህ ነው
?”
“
ትክክለኛው እድሜየን ስንት ገምተኸው ነው
?”
አልሁት
::
”
እንጃ
!
ብቻ ፎቶህን ሳየው ያልማዝ ኢዮቤልዩ ሊከበርለት የሚገባ ፊት ነው ያለህ”
“
ስነስርአት
!”
አልኩ በንዴት ጦፌ
::
”
ራስህ ስነስርአት
!!
ቀለም በወፍ ላባ እያጣቀስክ ግጥም የፃፍህ ሼባ ሰላሳ ሰባት ነኝ ስትል ትንሽ ሼም ነገር አይቆነጥጥህም
? ?”
Blocked
ከጀርባየ የተቀመጡ ሁለት ተስተናጋጆች ወሬውንና ምግቡን ጎንለጎን ሲያስኬዱት ሰማሁ
::
”
ብላ እንጂ
!”
ይላል አንደኛው
“
ዘጋኝ ባክህ
!
እኔ ፍቅር ሲይዘኝ ካንድ ክትፎ በላይ መብላት አልቺልም”
ከጥቂት ደቂቃ በኃላ ዘፈን ተጀመረ
::
አየ
!!
ዘፈን ሚሊኒየም አዳራሽ ቀረ
!!
የመዝፈኛይቱ መድረክ በጣም ትንሽ ከመሆኗ የተነሳ ዘፋኙ በእናቱ የሽንኩርት መክተፍያ ላይ ቆሞ የሚዘፍን ይመስላል
::
ከዘፋኙ ጀርባ ኪቦርድ ተጨዋቹ አቀርቅሯል
::
የሙዚቃ ተጫዋች ሳይሆን የመንደር ልብስ ሰፊ ነው የሚመስለው
::
ከጎኑ የግእዙን አስር ቁጥር የሚመስል ሰውየ ባለ እጄታ ሳንዱቅ የመሰለ ግብዳ ጊታር ተሸክሞ ቁሟል
::
ከጊታሩ የሚመነጭ ድምፅ አልሰማሁም
::
የሆነ ባልደረባው ” ሽንቴን ሸንቼ እስክመጣ ይህንን ጊታር ይዘህልኝ ቆይ” ብሎት የሄደ ነው የሚመስለው
::
በመድረኩና በተመጋቢው ማሃል መለስተኛ ዙ ሃያዘጠኝ የሚመስል ድምፅ ማጉያ ተጠምዷል
::
የዘፋኙን ድምፅ ብቻ ሳይሆን ሀሳቡን ሳያጎላው አይቀርም
::
በሩ አጠገብ ጠብደል አፍሮ አሜሪካዊ እልፍኝ አስከልካይ ተከምሯል
::
ሰውነቱ ግዙፍ ሲሆን ዘለግ ያለ ፂም አለው
::
ካንገት በታች ነፃ ትግል ታጋይ
–
ካንገት በላይ አቡነ አረጋይ
–
ነው ማለት ይቻላል
: :
የሚረብሽ ተስተናጋጅ ፍለጋ አይኑ በየማእዘኑ ይንከራተታል
::
ብዙ አልቆየም
::
አንድ
stress
የተጫወተበት አጭር ሰካራም ወደመድረኩ መጥቶ “ካሽ ስላልያዝኩ ነው
!
በክሬዲት ካርድ ብሸልምህ ይደብርሃል
?”
እያለ ዘፋኙን መበጥበጥ ጀመረ
::
አስከልካዩ በኮሌታው አንጠልጥሎ ይዞት ወጣ
::
ሳየው የመኪና ቁልፍ እንጂ ሰው ከነ ጭንቀቱ ያንጠለጠለ አይመስልም
::
ከብዙ ዘመን የቅምቀማ ልምዴ እንደተረዳሁት ከረጅም ቀምቃሚዎች ይልቅ አጫጭር ቀምቃሚዎች ፈጥነው ይሰክራሉ
::
ምክንያቱም አልኮል ረጅም ሰው ጭንቅላት ላይ ለመድረስ ብዙ ርቀት መራመድ አለበት
::
ሂሳብ ከፍየ እጄን ታጥቤ ልወጣ ሽንትቤት ገባሁ
::
ከጀርባየ ሁለት ሰዎች ጎንለጎን ቆመው ይሸናሉ
::
አንደኛው አርፎ በመሽናት ፋንታ በድንበርተኛው ሸኚ ላይ አስተያየት አይሉት ጥያቄ ሰነዘረ
::
“
ፍሬንድ በመጥረቢያ ነው እንዴ የተገረዝከው
?”
ድንገት ስልኬ ጠራ
::
አደይ ናት
::
አደይ የዛሬ አራት አመት አብራኝ መጥታ ጥገኝነት የጠየቀች ባለንጀራየ ናት
::
“
Birthday boy
የት ነው ያለኸው
?”
አለቺኝ
ያለሁበትን ተናገርኩ
::
“
እንዳትወጣ ጠብቀኝ”
እንሆ በመጨረሻ
!!!
ይሄን ላልማዝ ኢዮቤልዩ የታጨ ፊቴን ለሰርፕራይዝ አሰናድቼ ጠበቅሁ
::
ምንም ማድረግ አይቻልም
::
እድሌ ነው
::
ወንዶች ይታገሉህ ሴቶች ያገልግሉህ ተብየ የተፈጠርኩ ነኝ
::
ከጥቂት ደቂቃ በሁዋላ አደይ መጣች
ትንሽ ስናወጋ ቆየና ከቦርሳዋ የሆነ ጥቅል አወጣች
:: I knew it
ይላል ፈረንጂ
!!
ምን የመሰለ
I phone 7
ከፊቴ ቦገግ አለ
::
“
እንዴው ቆይ ምን አሳሰበሽ ” ብየ ልጠመጠምባት ስል ቀደመቺኝ
::
“
ወደ ኢትዮጵያ ስትመለስ ይህን ስልክ ለታናሽ ወንድሜ ትሰጥልኛለህ””
Share this:
Telegram
WhatsApp
Tweet
Like this:
Like
Loading...
%d