ባለፈው ሐሙስ በዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምበሲ፣ ዶ/ር አዲሱ ገብረ/እግዚአብሄር የኢትዮጵያ ሠብዓዊ መብት ከሚሽን ኰሚሽነር፣ የአገሪቱን የመብት አያያዝ ሪፖርት ያቀረቡበት አንድ ስብሰባ ተካሂዶ ነበር።

ስብሰባውን የጠራው በኢትዮጵያ መንግሥት ተቀጥሮ ይሠራል የተባለው/SGRLLC/ የተባለው ሎቢስት/አግባቢ/ ቡድን መሆኑም ታውቋል። በስብሰባው ላይ ለመገኘት ከሄዱ ኢትዮጵያውያን መካከል አንዳንዶቹ ከገቡ በኋላ እንዲወጡ የተደረጉ ሲሆን፣ ሌሎች ደግሞ ከብዙ ጭቅጭቅ በኋላ ቢገቡም ጥያቄ የማቅረብ ዕድል እንደተነፈጉ ተናግረዋል።

ለማድመጥ ይህን ተጫኑት⇓

https://ethiopanorama.comwp-content/uploads/2017/07/93b0ed24-1362-4cdc-be22-0fca1f3828a3_32k-1.mp3