August 4, 2017 – 

ቆንጅት ስጦታው

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እና ዳንኤል ሺበሺ፣ በድጋሚ

ለብይን ተቀጠሩ!

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እና አቶ ዳንኤል ሺበሺ በዚህ ክስ እያንዳንዳቸው አምሳ ሺህ ብር ዋስትና ማስያዣ እንዳቀረቡ ይታወቃል ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የመምህር በቀለ ገርባ የዋስትና መብታቸውን በተመለከተ በተደጋጋሚ ቀጠሮ ተይዞበት የነበረው ጉዳይ ዛሬም መፍትሔ ሳይሰጠው በድጋሚ ተለዋጭ ቀጠሮ ሊሰጥ ችሏል። መምህር በቀለ ገርባ የተመሰረተባቸው የሽብር ወንጀል ክስ ወደ መደበኛ የወንጀል ሕግ ተቀይሮ እንዲከላከል ውሳኔ መሰጠቱ የሚታወቅ ነው። በዚሁ መሠረት መምህር በቀለ ገርባ የዋስትና ጥያቄያቸውን ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ያቀረቡ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ የዋስትና ጥያቄ የከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ተቃውሞ እና አስተያየት መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ የሰጠ ቢሆንም ፤ ፍርድ ቤቱ አሁንም በድጋሚ የቀረበለትን የዋስትና መብት ጥያቄ ውሳኔ መስጠት ያልቻለ ሲሆን፤ያፊታችን ማክሰኞ ነሀሴ 2 ቀን 2009 .ም ውሳኔ ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ፍርድ ቤቱ ሰጥቷል ።


(
ይድነቃቸው ከበደ)